በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአከራይ ተከራይ የቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ ስንታየሁ ወልደሚካኤል ምክክር ያስፈለገው በአዋጁ አተገባበር ዙርያ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የቤት ፍላጎትን ለማሳካት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ መንግስት ችግሩን ለመፍታት የተለያዩ አማራጮችን አቅርቧል።
በማህበር በማደራጀት የመኖርያ ቤት ፍላጎትን ለማሟላት ተሞክሯል ያሉት ሃላፊው ይሄ በቂ ባለመሆኑ የአከራይ ተከራይ ግንኙነትን በአዋጅ አስደግፎ ማስተዳደር ማስፈለጉን አንስተዋል።
አዲሱ አዋጅ የተረጋጋ የመኖሪያ ቤት ኪራይ እንዲኖር የሚያስችል እንደሆነ ሃላፊው አብራርተዋል።
ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪና በመሀል ውል ማቋረጥን አዋጁ ይከለክላል።
አዋጁ በክልሉ ስድስት የማዕከል ከተሞች ላይ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ