በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአከራይ ተከራይ የቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ ስንታየሁ ወልደሚካኤል ምክክር ያስፈለገው በአዋጁ አተገባበር ዙርያ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የቤት ፍላጎትን ለማሳካት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ መንግስት ችግሩን ለመፍታት የተለያዩ አማራጮችን አቅርቧል።
በማህበር በማደራጀት የመኖርያ ቤት ፍላጎትን ለማሟላት ተሞክሯል ያሉት ሃላፊው ይሄ በቂ ባለመሆኑ የአከራይ ተከራይ ግንኙነትን በአዋጅ አስደግፎ ማስተዳደር ማስፈለጉን አንስተዋል።
አዲሱ አዋጅ የተረጋጋ የመኖሪያ ቤት ኪራይ እንዲኖር የሚያስችል እንደሆነ ሃላፊው አብራርተዋል።
ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪና በመሀል ውል ማቋረጥን አዋጁ ይከለክላል።
አዋጁ በክልሉ ስድስት የማዕከል ከተሞች ላይ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ