በቡርጂ ዞን ሶያማ ዙሪያ ወረዳ የወጣቶች አደረጃጀት ማጠናከርና መልሶ ማደራጀት የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል ።
ሰላምና ደህንነት ላይ ወጣቶችን በማሰማራት ችግሮች እንዳይከሰቱ በቅድሚያ መሰራት እንዳለበት የገለጹት የቡርጂ ዞን ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን አኖ ለዚህም በየመድረኮቹ በማሳተፍ ማወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በዞኑ ወጣቶች ሰላምን ከማስከበር አኳያ ሰፊ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው በበዓላት ወቅት ያሳዩት ተግባር የሚበረታታ እና የሚደገፍ እንደሆነ በመግለፅ ሁሉም ወጣቶች ለሰላም መቆም እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
የነገ ተተኪ አመራር የዛሬ ወጣቶች ናቸው ያሉት የሶያማ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሽብሩ ኦቴ ያላቸውን እምቅ ችሎታ እና ክሂሎት በመጠቀም ለነገ ማብቃት ያስፈልጋል ብለው፣ ዛሬ ላይ ያሉ ወጣቶችም የተሰጣቸውን ተልዕኮ በመውሰድ ለሀገር ሰላም እና ልማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የንቅናቄ መድረኩ ተሳታፊ ወጣቶች እንደተናገሩት፣ ወጣቶች የተሻለ ስራ ሲሰሩ ማበረታታት እና መደገፍ ያስፈልጋል፤ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ አለባቸው።
የወጣቶች ሊግ፣ ፌደሬሽን እና ማህበር ስም ብቻ ሆነው መቅረት እንደሌለባቸውና የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላትም ከተሟላ አገልግሎት ጋር ለወጣቶች ክፍት መሆን እንደሚገቡም ወጣቶቹ ተናግረዋል።
ዘጋቢ : አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ