በቡርጂ ዞን ሶያማ ዙሪያ ወረዳ የወጣቶች አደረጃጀት ማጠናከርና መልሶ ማደራጀት የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል ።
ሰላምና ደህንነት ላይ ወጣቶችን በማሰማራት ችግሮች እንዳይከሰቱ በቅድሚያ መሰራት እንዳለበት የገለጹት የቡርጂ ዞን ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን አኖ ለዚህም በየመድረኮቹ በማሳተፍ ማወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በዞኑ ወጣቶች ሰላምን ከማስከበር አኳያ ሰፊ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው በበዓላት ወቅት ያሳዩት ተግባር የሚበረታታ እና የሚደገፍ እንደሆነ በመግለፅ ሁሉም ወጣቶች ለሰላም መቆም እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
የነገ ተተኪ አመራር የዛሬ ወጣቶች ናቸው ያሉት የሶያማ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሽብሩ ኦቴ ያላቸውን እምቅ ችሎታ እና ክሂሎት በመጠቀም ለነገ ማብቃት ያስፈልጋል ብለው፣ ዛሬ ላይ ያሉ ወጣቶችም የተሰጣቸውን ተልዕኮ በመውሰድ ለሀገር ሰላም እና ልማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የንቅናቄ መድረኩ ተሳታፊ ወጣቶች እንደተናገሩት፣ ወጣቶች የተሻለ ስራ ሲሰሩ ማበረታታት እና መደገፍ ያስፈልጋል፤ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ አለባቸው።
የወጣቶች ሊግ፣ ፌደሬሽን እና ማህበር ስም ብቻ ሆነው መቅረት እንደሌለባቸውና የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላትም ከተሟላ አገልግሎት ጋር ለወጣቶች ክፍት መሆን እንደሚገቡም ወጣቶቹ ተናግረዋል።
ዘጋቢ : አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ