ባለፋት 10 ቀናት 4 የሱፐርቪዥን ቡድኖችን በማዋቀር በሁሉም ዞኖች ያሰማራው የማህበራዊ ክላስተር የታዩ መልካም ጎኖችንና ክፍተቶችን የሚገመግም የግብረ መልስ መድረክ ነው በወራቤ ከተማ እያካሄደ ያለው።
በሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ቅኝት ያደረገው የሱፐርቪዥን ቡድኑ በጤና በትምህርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ገምግሟል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የትምህርት ቢሮ ኃላፊውና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪው አቶ አንተነህ ፈቃዱ የተመራው የግብረ መልስ መድረክ ክልሉ ሞዴል ሆኖ እንዲወጣ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ እየመከረ ነው።
በሁሉም ዘርፎች የሚታዩ ክፍተቶችን በመፍታት ተሞክሮዎችን ደግሞ ወደ ሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በቀጣይ ሁለንተናው ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት መሰራት እንዳለበትም ተመላክቷል።
ዘጋቢ : ባዬ በልስቲ
More Stories
የምክር ቤቶችን አቅም በማጎልበት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ተናገሩ
ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ በማዋልና ገዢ ትርክትን በማስረጽ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማስተዋወቅ እንደሚገባ ተገለጸ
በምግብ ሰብል ራስን የመቻል አቅም ማሳደግ ላይ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ