ባለፋት 10 ቀናት 4 የሱፐርቪዥን ቡድኖችን በማዋቀር በሁሉም ዞኖች ያሰማራው የማህበራዊ ክላስተር የታዩ መልካም ጎኖችንና ክፍተቶችን የሚገመግም የግብረ መልስ መድረክ ነው በወራቤ ከተማ እያካሄደ ያለው።
በሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ቅኝት ያደረገው የሱፐርቪዥን ቡድኑ በጤና በትምህርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ገምግሟል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የትምህርት ቢሮ ኃላፊውና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪው አቶ አንተነህ ፈቃዱ የተመራው የግብረ መልስ መድረክ ክልሉ ሞዴል ሆኖ እንዲወጣ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ እየመከረ ነው።
በሁሉም ዘርፎች የሚታዩ ክፍተቶችን በመፍታት ተሞክሮዎችን ደግሞ ወደ ሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በቀጣይ ሁለንተናው ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት መሰራት እንዳለበትም ተመላክቷል።
ዘጋቢ : ባዬ በልስቲ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ