ባለፋት 10 ቀናት 4 የሱፐርቪዥን ቡድኖችን በማዋቀር በሁሉም ዞኖች ያሰማራው የማህበራዊ ክላስተር የታዩ መልካም ጎኖችንና ክፍተቶችን የሚገመግም የግብረ መልስ መድረክ ነው በወራቤ ከተማ እያካሄደ ያለው።
በሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ቅኝት ያደረገው የሱፐርቪዥን ቡድኑ በጤና በትምህርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ገምግሟል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የትምህርት ቢሮ ኃላፊውና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪው አቶ አንተነህ ፈቃዱ የተመራው የግብረ መልስ መድረክ ክልሉ ሞዴል ሆኖ እንዲወጣ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ እየመከረ ነው።
በሁሉም ዘርፎች የሚታዩ ክፍተቶችን በመፍታት ተሞክሮዎችን ደግሞ ወደ ሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በቀጣይ ሁለንተናው ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት መሰራት እንዳለበትም ተመላክቷል።
ዘጋቢ : ባዬ በልስቲ
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ