ባለፋት 10 ቀናት 4 የሱፐርቪዥን ቡድኖችን በማዋቀር በሁሉም ዞኖች ያሰማራው የማህበራዊ ክላስተር የታዩ መልካም ጎኖችንና ክፍተቶችን የሚገመግም የግብረ መልስ መድረክ ነው በወራቤ ከተማ እያካሄደ ያለው።
በሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ቅኝት ያደረገው የሱፐርቪዥን ቡድኑ በጤና በትምህርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ገምግሟል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የትምህርት ቢሮ ኃላፊውና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪው አቶ አንተነህ ፈቃዱ የተመራው የግብረ መልስ መድረክ ክልሉ ሞዴል ሆኖ እንዲወጣ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ እየመከረ ነው።
በሁሉም ዘርፎች የሚታዩ ክፍተቶችን በመፍታት ተሞክሮዎችን ደግሞ ወደ ሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በቀጣይ ሁለንተናው ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት መሰራት እንዳለበትም ተመላክቷል።
ዘጋቢ : ባዬ በልስቲ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ