የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ በክልሉ ይህን ክፍተት ለመድፈን ያለመ ስልጠና በሾኔ ከተማ መስጠት ጀምሯል።
የቢሮው ምክትል ሀላፊና የተቋማት አቅም ግንባታና ስልጠና ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ፈርሻ እንደገለፁት ሀገሪቷ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የገዛቻቸው ማሽኖች ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ አይደለም።
በዚህም እንደሀገር ከፍተኛ ኪሳራ እያስተናገድን ነው ያሉት ምክትል ሀላፊው በክልሉ ባሉ 38 የቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ኮሌጆች ውስጥ ያሉ ማሽነሪዎችን በአግባቡ በመጠቀም ለታለመለት አላማ ማዋል ይገባል ብለዋል።
የተገዙ ማሽኖች ከመጡ በኋላ አገልግሎት ላይ ሳይውሉ ለበርካታ አመታት መጋዘን ውስጥ መቀመጣቸው ሌላኛው ችግር መሆኑን ተናግረው ይህም መቀረፍ አለበት ብለዋል።
እየተሰጠ ያለው ስልጠናም በየኮሌጁ ያሉ ማሽነሪዎች ወደ ስራ ገብተው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
ስልጠናው ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ እና ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በመጡ አሰልጣኞች እየተሰጠ ነው።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ