የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ በክልሉ ይህን ክፍተት ለመድፈን ያለመ ስልጠና በሾኔ ከተማ መስጠት ጀምሯል።
የቢሮው ምክትል ሀላፊና የተቋማት አቅም ግንባታና ስልጠና ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ፈርሻ እንደገለፁት ሀገሪቷ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የገዛቻቸው ማሽኖች ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ አይደለም።
በዚህም እንደሀገር ከፍተኛ ኪሳራ እያስተናገድን ነው ያሉት ምክትል ሀላፊው በክልሉ ባሉ 38 የቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ኮሌጆች ውስጥ ያሉ ማሽነሪዎችን በአግባቡ በመጠቀም ለታለመለት አላማ ማዋል ይገባል ብለዋል።
የተገዙ ማሽኖች ከመጡ በኋላ አገልግሎት ላይ ሳይውሉ ለበርካታ አመታት መጋዘን ውስጥ መቀመጣቸው ሌላኛው ችግር መሆኑን ተናግረው ይህም መቀረፍ አለበት ብለዋል።
እየተሰጠ ያለው ስልጠናም በየኮሌጁ ያሉ ማሽነሪዎች ወደ ስራ ገብተው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
ስልጠናው ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ እና ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በመጡ አሰልጣኞች እየተሰጠ ነው።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ