ሀዋሳ: ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢድ አልፈጥር በዓልን በፍቅርና በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር ተናገሩ::
1ሺ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሀዋሳ ከተማ ሚሊኒየም አደባባይ ተከብሯል::
በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበት በዓል ነው ብለዋል::
በዚሁ ወቅት በአካባቢያችን ያሉ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ከሁሉም ጋር በፍቅር ማሳለፍ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የኬሌ ከተማ አስተዳደር ለአቅመ ደካሞችና ወላጅ አልባ ህፃናት የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ማስተር አብነት ከበደ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
“የአጉራሽን እጅ ነካሽ”