የኢድ አልፈጥር በዓልን በፍቅር እና በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ ተገለፀ

ሀዋሳ: ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢድ አልፈጥር በዓልን በፍቅርና በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር ተናገሩ::

1ሺ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሀዋሳ ከተማ ሚሊኒየም አደባባይ ተከብሯል::

በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበት በዓል ነው ብለዋል::

በዚሁ ወቅት በአካባቢያችን ያሉ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ከሁሉም ጋር በፍቅር ማሳለፍ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ