ሀዋሳ: ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢድ አልፈጥር በዓልን በፍቅርና በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር ተናገሩ::
1ሺ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሀዋሳ ከተማ ሚሊኒየም አደባባይ ተከብሯል::
በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበት በዓል ነው ብለዋል::
በዚሁ ወቅት በአካባቢያችን ያሉ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ከሁሉም ጋር በፍቅር ማሳለፍ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ