ሀዋሳ: ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢድ አልፈጥር በዓልን በፍቅርና በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር ተናገሩ::
1ሺ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሀዋሳ ከተማ ሚሊኒየም አደባባይ ተከብሯል::
በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱሽኩር አብዱልቃድር፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበት በዓል ነው ብለዋል::
በዚሁ ወቅት በአካባቢያችን ያሉ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ከሁሉም ጋር በፍቅር ማሳለፍ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ