በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ 1 ሺህ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል እየተከበረ ነው

ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታላቁን የረመዳን ወር ለ30 ቀናት ዱኣ በማድረግ፣ በጾምና በሰላት ያሳለፈው ህዝበ ሙስሊሙ፥ ኢድ አልፈጥርን በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው።

1 ሺህ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው፡፡

በዓሉ በወራቤ ስታዲየም ሲከበር የዕምነቱ ተከታዮች የኢድ ሰላት ስነ-ስርዓት በማካሔድ፥ ከቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤቶቻቸው ጋር በመሆን በዓሉን በማክበር ላይ ናቸው፡፡

ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ