ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታላቁን የረመዳን ወር ለ30 ቀናት ዱኣ በማድረግ፣ በጾምና በሰላት ያሳለፈው ህዝበ ሙስሊሙ፥ ኢድ አልፈጥርን በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው።
1 ሺህ 445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው፡፡
በዓሉ በወራቤ ስታዲየም ሲከበር የዕምነቱ ተከታዮች የኢድ ሰላት ስነ-ስርዓት በማካሔድ፥ ከቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤቶቻቸው ጋር በመሆን በዓሉን በማክበር ላይ ናቸው፡፡
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ