ህዝበ ሙስሊሙ በረመዳን ወር ያሳያቸውን የበጎነት እሴቶችን በቀጣይ በመደበኛ ተግባራቸው አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል – አቶ ፀጋዬ ማሞ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ማሞ ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች ለ1 ሺህ 445ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸው ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር በረመዳን ወቅት ያሳየውን አብሮነት በማጠናከር አቅመ ደካሞችን በማገዝና በመንከባከብ፣ የታመሙትን በመጠየቅ፣ በዓሉን ማክበር እንዳለባቸውም ገልጸዋል።
በዓሉ የመተዛዘን፣ የመረዳዳት እና የአብሮነት ዕሴት የሚገለጽበት መሆኑን የገለጹት አቶ ፀጋዬ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በረመዳን ወር ያከናወናቸውን መልካም ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።
ህዝበ ሙስሊሙ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ልማትን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት እያበረከቱ ያለውን አስተዋፅኦ ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያን ከፍታን ማፅናት የሚያስችሉ ተምሳሌቶችን በመውሰድ ውስጣዊ አንድነትን ከሚሸረሽሩ ጉዳዮች መራቅ ያስፈልጋል ያሉት አቶ ፀጋዬ በኀብረ ብሔራዊ አንድነት የኢትዮጵያን ብልፅግና ማረጋገጥ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ የሰላም፣የጤና፣የአንድነት እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ዒድ ሙባረክ!
መልካም በዓል!
አቶ ፀጋዬ ማሞ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ