የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሁሉንም የጋራ ጥረት የሚሻ መሆኑ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በአመለካከትና በተግባር የተግባባ የብልጽግና አመራር መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ዞናዊ የአመራር የውይይት መድረክ በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩ ከዚህ ቀደም በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና በዞን ማዕከል አመራሮች የተካሄደ ሲሆን አጠቃላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የዞኑ ተወላጅ አመራሮችን ያጠቃለለ ነው።
በመድረኩም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤልን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ