የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሁሉንም የጋራ ጥረት የሚሻ መሆኑ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በአመለካከትና በተግባር የተግባባ የብልጽግና አመራር መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ዞናዊ የአመራር የውይይት መድረክ በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩ ከዚህ ቀደም በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና በዞን ማዕከል አመራሮች የተካሄደ ሲሆን አጠቃላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የዞኑ ተወላጅ አመራሮችን ያጠቃለለ ነው።
በመድረኩም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤልን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ