የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሁሉንም የጋራ ጥረት የሚሻ መሆኑ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በአመለካከትና በተግባር የተግባባ የብልጽግና አመራር መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ዞናዊ የአመራር የውይይት መድረክ በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩ ከዚህ ቀደም በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና በዞን ማዕከል አመራሮች የተካሄደ ሲሆን አጠቃላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የዞኑ ተወላጅ አመራሮችን ያጠቃለለ ነው።
በመድረኩም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤልን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ