በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የተሰናዳው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽን በይፋ ተከፈተ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የተሰናዳው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽን በክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተጎብኝቷል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የኢንቨስትመንት፣ ኢንዱስትሪና የግብርና ልማት ውጤቶች በኤግዚቢሽኑ ለዕይታ የቀረቡ ሲሆን፥ የማኑፋክቸሪንግ ልማት ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ስኬት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ለማስቻል የግሉ ዘርፍ እንዲጎለብትና የዕድገት አማራጮችን ለማስፋት አስተዋጽኦ እንዳለው ተመልክቷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤልን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ መንግስት የስራ ኃላፊዎች በጉብኝቱ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ