“ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እንዳሻው ጣሰው እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ከክልሉ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ የፓርቲው አባላት በኮንፍረንሱ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የኮንፍራንሱ አላማም በዋናነት ፓርቲው ለህዝብ የገባውን ቃል ከልማት አንፃር ምን ተሰራ ምንስ ይቀራል የሚለውን በስፍት ለመመልከት ያግዛል ተብሏል።
ኮንፍረንሱ ከቀበሌ ጀምሮ በየመዋቅሩ ሲካሄድ የመጣና ይህም ክልላዊ ማጠቃለያ ነው።
በኮንፍረንሱም ከ1ሺ በላይ የክልሉ የፓርቲው አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ቃልአብ ጸጋዬ

More Stories
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ባለፉት ጊዜያት ከህዝብ ለተነሱ ጥያቄዎች መንግስት ምላሽ እየሰጠ መቆየቱ ተገለጸ