“ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እንዳሻው ጣሰው እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ከክልሉ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ የፓርቲው አባላት በኮንፍረንሱ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የኮንፍራንሱ አላማም በዋናነት ፓርቲው ለህዝብ የገባውን ቃል ከልማት አንፃር ምን ተሰራ ምንስ ይቀራል የሚለውን በስፍት ለመመልከት ያግዛል ተብሏል።
ኮንፍረንሱ ከቀበሌ ጀምሮ በየመዋቅሩ ሲካሄድ የመጣና ይህም ክልላዊ ማጠቃለያ ነው።
በኮንፍረንሱም ከ1ሺ በላይ የክልሉ የፓርቲው አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ቃልአብ ጸጋዬ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ