“ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ቃል በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እንዳሻው ጣሰው እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ከክልሉ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ የፓርቲው አባላት በኮንፍረንሱ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የኮንፍራንሱ አላማም በዋናነት ፓርቲው ለህዝብ የገባውን ቃል ከልማት አንፃር ምን ተሰራ ምንስ ይቀራል የሚለውን በስፍት ለመመልከት ያግዛል ተብሏል።
ኮንፍረንሱ ከቀበሌ ጀምሮ በየመዋቅሩ ሲካሄድ የመጣና ይህም ክልላዊ ማጠቃለያ ነው።
በኮንፍረንሱም ከ1ሺ በላይ የክልሉ የፓርቲው አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ቃልአብ ጸጋዬ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ