“ኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች ውብ ናት” – ዶ/ር አለሙ ስሜ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሀምበርቾ 777 የጎበኙት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ ዘርፈ ብዙ ትርጉምና ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
777ቱንም የተራራው መውጫ ደረጃዎችን ተራሞደው ተራራው አናት ላይ የወጡት ሚኒስትሩ “ኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች ውብ ናት” ሲሉ ተናግረዋል። “ደረጃውን ወጥቼ በመጨረሴም ደስ ብሎኛል” ነው ያሉት ሚኒስትሩ።
በሀገራችን በርካታ ተራራዎችና የሚያምሩ መልክዓ ምድሮችን አልምተን የቱሪዝም የገቢ ምንጭ ማድረግ እየተቻለ ነገር ግን ለበርካታ አመታት ሳንጠቀምበት ቀርተናል ሲሉ ገልጸዋል።
ከለውጡ ወዲህ በተለይም ጠቅላ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ከግቢያቸው ጀምሮ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የኢትዮጵያን እምቅ የተፈጥሮ አቅም ማሳየት የቻለ፣ ገፅታዋን የቀየረና ቱሪስትን መሳብ የሚችል ሥራ ማከናወን ችለዋል ነው ያሉት ዶ/ር አለሙ ስሜ።
ሌሎችም በየደረጃው ያለን አመራሮች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ያለሟቸውን የቱሪዝም ፕሮጀክቶች በምሳሌነት በመውሰድ ለሀገር እድገት የሚጠበቅብንን ማበርከት ይኖርብናል ሲሉ አስገንዝበዋል።
የሀምበርቾ 777 ኢኮ ቱሪዝም የዚህ ማሳያ ነው ያሉት ዶ/ር ዓለሙ ታሪክ ያለው ለመዝናኛም ለጤናችንም የሚሆን ድንቅ ቦታ ነው ብለዋል።
አክለውም አሁንም ማረፊያ ሎጆች፣ ማደሪያ መኝታዎች እና በአካል ጉዳትም ሆነ በተለያዩ ችግሮች ተራራውን መውጣት ላልቻሉ ወገኖችም ምቹ ማድረግን እንደሚጠይቅ ተናግረዋል።
ከተሠራበት ከዚህ በላይ ውብና በርካታ ቱሪስት እንዲስብ ማድረግ ይቻላልም ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ