የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ከዞንና ከልዩ ወረዳ ስራ አስፈፃሚ አካላት ጋር በስራ አፈጻጸም ዙሪያ በጽህፈት ቤታቸው እየተወያዩ ነው
ሀዋሳ፡ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ከዞንና ከልዩ ወረዳ ስራ አስፈፃሚ አካላት ጋር በስራ አፈጻጸም ዙሪያ በጽህፈት ቤታቸው እየተወያዩ ይገኛል።
ርዕሰ መስተዳድሩ እየተወያዩ የሚገኙት በክልሉ ሰላምና ጸጥታ፣ በግብርና እንዲሁም በገቢ አሰባሰብ፤ በተሰሩ ስራዎች ላይ ነው።
በአጀንዳዎቹ ላይ ጥልቅ ውይይት ከተደረገ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል።

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ