በደቡብ ኦሞ ዞን አገራዊ ምክክር ለአገራዊ መግባባት በሚል መርህ ሲካሄድ የቆየው የየማህበረሰብ ተወካዮች ምርጫ መጠናቀቁን አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ
በማጠቃለያው መርሃግብር በዞኑ በ3 ወረዳዎች የሚኖሩ ማህበረሰብ ክፍሎች በኮሚሽኑ የሚሳተፉ ተወካዮቻቸውን ምርጫ አካሂደዋል።
በዞኑ ቱርሚ ከተማ ለሁለት ተከታይ ቀናት ሲካሄድ በቆየው የየማህበረሰብ ተወካዮች ምርጫ ሂደት ማጠቃለያን በተመለከተ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ዮናስ አዳዬ እንደገለፁት የሀገራዊ ምክክር ዋነኛ ግብ እንደአገር ያልተግባባንባቸዉን መሠረታዊ ጉዳዮችን በመለየት፣ መንስኤዎቻቸዉን ነቅሶ በማዉጣት በመነጋገርና በመመካከር የጋራ መግባባት መፍጠር የሚቻልበት ሂደት ነዉ።
በኢትዮጵያ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ የፖለቲካና የሐሳብ መሪዎች እንዲሁም ከአገር ዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ተዉልደ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ስለአገሩ በሚደረገው ምክክር በዉክልና ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
ኮሚሽነሩ አያይዘዉም አካታች አገራዊ ምክክሮችን ማካሄድ የተሻለ አገራዊ መግባባትን ለመገንባት በሂደትም የመተማመንና ተቀራርቦ የመሥራት ባህልን ለማጎልበትና የተሸረሸሩ ማህበራዊ እሴቶችን ለማደስ እንደሚጠቅም ይታመንበታል ብለዋል።
አገራዊ ምክክር ከሌሎች ግጭት መፍቻ መንገዶች በተለየ መልኩ በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ መስማማት ላይ ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ ለሆኑ እና መተማመንን ለሚፈጥሩ መግባባቶች መደላድል የሚያበጅ እንደሆነም ኮሚሽነሩ አሰረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ