ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ተሰናበቱ
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ራሳቸውን አንስተዋል።
የ65 ዓመቱ አሰልጣኝ እኤአ በ2021 ላዚዮን በዋና አሰልጣኝነት የተረከቡ ሲሆን በያዝነው የውድድር ዓመት የጣሊያን ርዕሰ መዲናውን ክለብ ውጤታማ ማድረግ ባለመቻላቸው ሃላፊነቱን ለቀዋል።
ላዚዮ በሴሪአው ከ28 ጨዋታዎች በ12ቱ ተሸንፎ 40 ነጥቦችን በመያዝ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ማውሪዚዮ ሳሪ ላዚዮን ከማሰልጠናቸው በተጨማሪ ኢምፖሊን፥ናፖሊን፥ቼልሲን እንዲሁም ዩቬንቱስን በአሰልጣኝነት መምራታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ማንቸስተር ሲቲ በአዲሱ የውድድር ዓመት 2ኛ ተከታታይ ሽንፈት አስተናገደ
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል
ጄሚ ቫርዲ ወደ ጣሊያን ሴሪኣ ሊያቀና ነው