ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ተሰናበቱ
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ራሳቸውን አንስተዋል።
የ65 ዓመቱ አሰልጣኝ እኤአ በ2021 ላዚዮን በዋና አሰልጣኝነት የተረከቡ ሲሆን በያዝነው የውድድር ዓመት የጣሊያን ርዕሰ መዲናውን ክለብ ውጤታማ ማድረግ ባለመቻላቸው ሃላፊነቱን ለቀዋል።
ላዚዮ በሴሪአው ከ28 ጨዋታዎች በ12ቱ ተሸንፎ 40 ነጥቦችን በመያዝ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ማውሪዚዮ ሳሪ ላዚዮን ከማሰልጠናቸው በተጨማሪ ኢምፖሊን፥ናፖሊን፥ቼልሲን እንዲሁም ዩቬንቱስን በአሰልጣኝነት መምራታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል