ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ተሰናበቱ
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ራሳቸውን አንስተዋል።
የ65 ዓመቱ አሰልጣኝ እኤአ በ2021 ላዚዮን በዋና አሰልጣኝነት የተረከቡ ሲሆን በያዝነው የውድድር ዓመት የጣሊያን ርዕሰ መዲናውን ክለብ ውጤታማ ማድረግ ባለመቻላቸው ሃላፊነቱን ለቀዋል።
ላዚዮ በሴሪአው ከ28 ጨዋታዎች በ12ቱ ተሸንፎ 40 ነጥቦችን በመያዝ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ማውሪዚዮ ሳሪ ላዚዮን ከማሰልጠናቸው በተጨማሪ ኢምፖሊን፥ናፖሊን፥ቼልሲን እንዲሁም ዩቬንቱስን በአሰልጣኝነት መምራታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በወልቂጤ ከተማ የሰርከስ ስፖርት ምልመላና የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት መርሃ ግብር ተካሄደ
አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል እንግሊዝ ወደ ፍፃሜ ባለማለፏ ከፍተኛ ትችትን አስተናገዱ
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ