ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ተሰናበቱ
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ከላዚዮ አሰልጣኝነት በገዛ ፈቃዳቸው ራሳቸውን አንስተዋል።
የ65 ዓመቱ አሰልጣኝ እኤአ በ2021 ላዚዮን በዋና አሰልጣኝነት የተረከቡ ሲሆን በያዝነው የውድድር ዓመት የጣሊያን ርዕሰ መዲናውን ክለብ ውጤታማ ማድረግ ባለመቻላቸው ሃላፊነቱን ለቀዋል።
ላዚዮ በሴሪአው ከ28 ጨዋታዎች በ12ቱ ተሸንፎ 40 ነጥቦችን በመያዝ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ማውሪዚዮ ሳሪ ላዚዮን ከማሰልጠናቸው በተጨማሪ ኢምፖሊን፥ናፖሊን፥ቼልሲን እንዲሁም ዩቬንቱስን በአሰልጣኝነት መምራታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል የክርስቲያን ኮፋኔን የዝውውር ሁኔታ መከታተል ጀመረ
ፈረንሳይ ስፔንን በመብለጥ በወቅታዊ የሀገራት ደረጃ ቀዳሚ ሆነች
ስፖርት ህዝባዊ መሠራት እንዲኖረው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ