ከ100 በላይ ግብር ከፋዮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን የጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 04/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በተደረገው የህግ ማስከበር ሥራ ከ100 በላይ ግብር ከፋዮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን የጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቋል።
የጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌቱ ታምሩ እንደተናገሩት መምሪያው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት መጋቢት 03 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው ኦፕሬሽን 6 ግብር ከፋዮች ግብር በማጭበርበርና ደረሰኝ ባለመስጠት በህግ ቁጥጥር ሥር ውለው የምርመራ ሥራ እየተከውነ መሆኑን አስታውቀዋል።
በተደረገው ድንገተኛ የታክስ ኦፕሬሽን በ107 ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰዳቸውን ጠቁመው ተግባሩ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።
የግብር ማጭበርበር ባደረጉ ግብር ከፋዮች ላይ በተደረገው የህግ ማስከበር ተግባር 1 ሚሊዮን 830 ሺህ 60 ብር ወደ መንግስት ካዝና ገቢ ተደርጎል ነው ያሉት፡፡
የክትትልና ህግን የማስከበሩ ሥራ በዞኑ ዲላ፣ ይርጋጨፌ እና ገደብ ከተሞች ላይ መካሄዱን ገልጸው ሕብረተስቡ ግብር የሚሰውሩ አካላት ላይ አስፈላጊውን ጥቆማ በመሰጠት የተጀመረውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን በቅንጅት መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ዘጋቢ:- ፅጌ ደምሴ ከይርጋጨፌ ጣቢያች።

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ