የኬሌ ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 5ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄደ
ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ዋና አፈ-ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ ሀና ኃይሌ ለከተማው ልማት ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ብለዋል።
ብልጽግናን ለማረጋገጥና ለዜጎች ኑሮ የሚመች ከተማ ለመፍጠር ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ መልካሙ አስፋው በቅርቡ ወደ ከተማ የታቀፉ ቀበሌያት አደረጃጀት ሞሽን ሰነድ አቅርበው አስቸኳይ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የኬሌ ከተማ ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ኃይሉ በበኩላቸው በከተማው ሥር ያሉ የቀበሌ ወሰን መካለል፣ የሰው ቁጥር መረጃና ስያሜ በታችኛው የቀበሌ ምክር ቤት እንደሚጸድቅ አስረድተዋል።
ከጉባኤው ተሳታፊዎች መካከል የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ የምክር ቤቱ አባል አቶ ፍጹም አራጋው እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት የቀበሌ አደረጃጀት የከተማውን ህብረተሰብ ጥያቄ የሚመልስ እንደሆነ ነው የተናገሩት፡፡
በከተማ አስተዳደሩ ሥር ባሉ ሴክተሮች ላይ ሹመት በማጽደቅ ጉባኤው ተጠናቋል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ