የኬሌ ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 5ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄደ
ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ዋና አፈ-ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ ሀና ኃይሌ ለከተማው ልማት ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ብለዋል።
ብልጽግናን ለማረጋገጥና ለዜጎች ኑሮ የሚመች ከተማ ለመፍጠር ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ መልካሙ አስፋው በቅርቡ ወደ ከተማ የታቀፉ ቀበሌያት አደረጃጀት ሞሽን ሰነድ አቅርበው አስቸኳይ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የኬሌ ከተማ ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ኃይሉ በበኩላቸው በከተማው ሥር ያሉ የቀበሌ ወሰን መካለል፣ የሰው ቁጥር መረጃና ስያሜ በታችኛው የቀበሌ ምክር ቤት እንደሚጸድቅ አስረድተዋል።
ከጉባኤው ተሳታፊዎች መካከል የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ የምክር ቤቱ አባል አቶ ፍጹም አራጋው እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት የቀበሌ አደረጃጀት የከተማውን ህብረተሰብ ጥያቄ የሚመልስ እንደሆነ ነው የተናገሩት፡፡
በከተማ አስተዳደሩ ሥር ባሉ ሴክተሮች ላይ ሹመት በማጽደቅ ጉባኤው ተጠናቋል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ