የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እየተወያየ ይገኛል
የኢንቨስትመንት መሬት የተላለፈበት መንገድና በሂደቱ የታዩ ችግሮች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል።
በክልሉ መስፈርት ያሟሉ 77 ፕሮጀክቶች መሬት እንዲሰጣቸው የሚል የውሳኔ ሃሳብ ኮሚቴው አቅርቧል።
ሌሎች አንዳንድ መስፈርቶችን ያላሟሉ 35 ኘሮጀክቶች ሟሟላት ያለባቸውን በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ሲያሟሉ መሬት እንዲሰጣቸው የሚል የውሳኔ ሃሳብ ቀርቧል።
29 ኘሮጀክቶች ውድቅ ተደርገዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የተጭበረበረ የባንክ ስቴትመንት ማቅረብ፣ የተዛባ መረጃ ማቅረብ፣ በዞን አካባቢ የተሰጠው የኢንቨስትመንት ፈቃድና ለክልሉ የሚላከው ሌላ ሆኖ መገኘት ጉዳዩን በተከታተለው ኮሚቴ የታዩ ችግሮች በሚል ተዘርዝሯል።
ኮሚቴው ግልፅ አሰራር፣ የህግ ማዕቀፍና ወጥ ስታንዳርድ መኖር አለበት የተባለ ሲሆን በመንግስትም ይሁን በባለሃብቱ በኩል ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ አካሄድ መከተል እንደሚገባ ኮሚቴው ጠቁሟል።
መስተዳድር ምክር ቤቱ በክልሉ የሰባት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ይመክራል።
የሰው ሃይል የመዋቅር ጥናት የደረሰበትን ደረጃ ይመለከታል፡፡ ልዩ ልዩ አዋጆችና ደንቦች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ለማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ