የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እየተወያየ ይገኛል
የኢንቨስትመንት መሬት የተላለፈበት መንገድና በሂደቱ የታዩ ችግሮች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል።
በክልሉ መስፈርት ያሟሉ 77 ፕሮጀክቶች መሬት እንዲሰጣቸው የሚል የውሳኔ ሃሳብ ኮሚቴው አቅርቧል።
ሌሎች አንዳንድ መስፈርቶችን ያላሟሉ 35 ኘሮጀክቶች ሟሟላት ያለባቸውን በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ሲያሟሉ መሬት እንዲሰጣቸው የሚል የውሳኔ ሃሳብ ቀርቧል።
29 ኘሮጀክቶች ውድቅ ተደርገዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የተጭበረበረ የባንክ ስቴትመንት ማቅረብ፣ የተዛባ መረጃ ማቅረብ፣ በዞን አካባቢ የተሰጠው የኢንቨስትመንት ፈቃድና ለክልሉ የሚላከው ሌላ ሆኖ መገኘት ጉዳዩን በተከታተለው ኮሚቴ የታዩ ችግሮች በሚል ተዘርዝሯል።
ኮሚቴው ግልፅ አሰራር፣ የህግ ማዕቀፍና ወጥ ስታንዳርድ መኖር አለበት የተባለ ሲሆን በመንግስትም ይሁን በባለሃብቱ በኩል ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ አካሄድ መከተል እንደሚገባ ኮሚቴው ጠቁሟል።
መስተዳድር ምክር ቤቱ በክልሉ የሰባት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ይመክራል።
የሰው ሃይል የመዋቅር ጥናት የደረሰበትን ደረጃ ይመለከታል፡፡ ልዩ ልዩ አዋጆችና ደንቦች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ለማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ