የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስፋት እየታየ ያለውን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መሥራት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የጌዴኦ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕሪይዞች ልማት መምሪያ ከኦሞ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር የሥራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ የኢኮኖሚ ችግርን ለመፍታትና የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም በቁጠባና ብድር አመላለስ ላይ የተጀመሩ የፖሊሲ ማስተካከያዎችን ተግባር ላይ በማዋል የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
በመድረኩ በኦሞ ባንክ የዲላ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ ጌታቸው በራሶ፣ የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ እና ሌሌች የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ብሔራዊ ምክክር ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባሻገር ችግሮችን በውይይትና በሀሳብ የበላይነት ለመፍታት መሠረት እንደሚጥል ተገለጸ
የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻ የማሳ ዝግጅት ቢያደርጉም በቂ ግብዓት አለማግኘታቸውን ገለጹ