የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስፋት እየታየ ያለውን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መሥራት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የጌዴኦ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕሪይዞች ልማት መምሪያ ከኦሞ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር የሥራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ የኢኮኖሚ ችግርን ለመፍታትና የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም በቁጠባና ብድር አመላለስ ላይ የተጀመሩ የፖሊሲ ማስተካከያዎችን ተግባር ላይ በማዋል የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
በመድረኩ በኦሞ ባንክ የዲላ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ ጌታቸው በራሶ፣ የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ እና ሌሌች የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ