የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስፋት እየታየ ያለውን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መሥራት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የጌዴኦ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕሪይዞች ልማት መምሪያ ከኦሞ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር የሥራ ዕድል ፈጠራ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ የኢኮኖሚ ችግርን ለመፍታትና የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም በቁጠባና ብድር አመላለስ ላይ የተጀመሩ የፖሊሲ ማስተካከያዎችን ተግባር ላይ በማዋል የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
በመድረኩ በኦሞ ባንክ የዲላ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ ጌታቸው በራሶ፣ የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ እና ሌሌች የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ