የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ዘርፍ ምክር ቤት እና የነጋዴ ሴቶች ማህበር ምስረታ እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ መጋቢት 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ዘርፍ ምክር ቤት እና የነጋዴ ሴቶች ማህበር ምስረታ መድረክ በሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠዉ በምስረታ መድረኩ ማስጀመሪያ ላይ እንደተናገሩት፤ የንግድና ዘርፍ ም/ቤት እና የነጋዴ ሴቶች ማህበር በሸማችና አምራች መሀል ተዋናይ በመሆን በመካከላቸው የሚደረገውን የገበያ ትስስር ምቹ ስርዓት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ናቸዉ።
ምክር ቤቶቹ በትክክለኛዉ አሰራርና ስርዓት የሚንቀሳቀሱ ከሆነ እንደ ሀገር የተጋረጠውን የኑሮ ዉድነት ለማረጋጋት ሁሉም ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን ሚናቸው የላቀ መሆኑን አመላክተዋል።
በምስረታ መድረኩ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ወይይት እየተደረገበት ሲሆን አዲስ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የንግድ ዘርፍ ም/ቤት ፕሬዝዳንት እና የነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ምርጫ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ የዞንና ልዩ ወረዳ የንግድና ገበያ ልማት ተቋማት ኃላፊዎች እና ነባር የንግድ ዘርፍ ፕሬዝዳንት እና የነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ