የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመለከቱ
ሀዋሳ: የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል::
የሾኔ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ2014 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው 83 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል::
በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮች ለክልሉ አመራር ገለፃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም ትኩረት ሰጥቶ በመሥራ ሊጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች በምልከታው ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች