የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመለከቱ
ሀዋሳ: የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል::
የሾኔ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ2014 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው 83 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል::
በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮች ለክልሉ አመራር ገለፃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም ትኩረት ሰጥቶ በመሥራ ሊጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች በምልከታው ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ