የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመለከቱ
ሀዋሳ: የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል::
የሾኔ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ2014 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው 83 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል::
በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮች ለክልሉ አመራር ገለፃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም ትኩረት ሰጥቶ በመሥራ ሊጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች በምልከታው ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የመልካም አስተዳደር ችግሮች ተቀርፈው ህብረተሰቡ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
በጉራጊኛ ቋንቋ የሚጻፉ መጽሐፍት ለቋንቋው እድገት፣ መልማት፣ መበልጸግና ወደ ትውልዱ ለማድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው – ረዳት ፕሮፌሰር ካሚል ኑረዲን
የ”ባለ ካዳቤ” በዓል የዕርቅ፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የብርሃን ተምሳሌት መሆኑ ተገለጸ