የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመለከቱ
ሀዋሳ: የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል::
የሾኔ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ2014 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው 83 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል::
በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮች ለክልሉ አመራር ገለፃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም ትኩረት ሰጥቶ በመሥራ ሊጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች በምልከታው ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ