ከሾኔ- አጀባ – ማዞሪያ ድረስ የተገነባው የጠጠር መንገድ ተመረቀ

ከሾኔ- አጀባ – ማዞሪያ ድረስ የተገነባው የጠጠር መንገድ ተመረቀ

ሀዋሳ: የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለሥልጣን ዱራሜ ዲስትሪክት የተገነባው ከሾኔ- አጀባ – ማዞሪያ ድረስ የተገነባው የ18 ኪ.ሜ መንገድ የጠጠር መንገድ ተመርቋል::

በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ መንገዱን በይፋ አስመርቀዋል::

በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ጨምሮ በምክል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም የክልል እና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ