ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል፡፡
ለዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላርስ ራስሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ሀገራቱ ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረት የሚሰጡ የረጅም ጊዜ ግንኙነቶችን የሚጋሩ መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ውይይታችን በርካታ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮችን ያካተተ ውጤታማ እንደነበርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ