ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል፡፡
ለዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላርስ ራስሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ሀገራቱ ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረት የሚሰጡ የረጅም ጊዜ ግንኙነቶችን የሚጋሩ መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ውይይታችን በርካታ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮችን ያካተተ ውጤታማ እንደነበርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ