ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል፡፡
ለዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላርስ ራስሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ሀገራቱ ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረት የሚሰጡ የረጅም ጊዜ ግንኙነቶችን የሚጋሩ መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ውይይታችን በርካታ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮችን ያካተተ ውጤታማ እንደነበርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።

More Stories
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን በመርታት ወደ አሸናፊነት ተመለሰ
በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት በመሳተፍ የሚፈልገውን መንግስት ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት ተገለጸ
ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው – አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል