ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ከዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል፡፡

ለዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላርስ ራስሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ሀገራቱ ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረት የሚሰጡ የረጅም ጊዜ ግንኙነቶችን የሚጋሩ መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ውይይታችን በርካታ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮችን ያካተተ ውጤታማ እንደነበርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት።