የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፌደራልና የክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች አባላት የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፌደራልና የክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች አባላት የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

ሀዋሳ: የካቲት 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፌዴራል ፓርላማ እና የክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች አባላት ከወከሏቸው ህዝብ ጋር ያደረጉት ውይይት ግብረ-መልስ ማቅረቢያ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው::

በውይይት መድረኩ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ፣ ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የሁለቱ ምክር ቤቶች የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ተገኝተዋል::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ