በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የዞኑ ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮናና 21ኛው የባህል ስፖርት ዉድድር ፍጻሜዉን አገኘ
በሻምፒዮናው በእግር ኳስ ለፍፃሜ በቀረቡት የቸሀ ወረዳና የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድኖች መካከል የተደረገው ጨዋታ በመደበኛው ሰአት በአቻ ውጤት ቢጠናቀቅም በመለያ ምት የቸሃ ወረዳ አምስት ለአራት በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።
ለደረጃ በተደረገ መርሃ ግብር የጉንችሬ ከተማና የእምድብር ከተማ አስተዳደር ባደረጉት ጨዋታ በተመሳሳይ በመለያ ምት እምድብር ከተማን አሸናፊ በማድረግ ሶሥተኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ አድርጎታል።
በሌሎች ዘርፎች በአትሌቲክስ የጌታ፣ በቦሊቦል አበሽጌ፣ በባህል ስፖርት ሙህር አክሊል፣ በቴኳንዶ ጉመር ወረዳን ሻምፒዮን ሲያደርግ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
በውድድሩ የመዝጊያ መርሀ ግብር የጉራጌ ዞንና የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር አመራር አካላት በክብር እንግድነት ታድመውበታል።
በውድድሩ የተሻለ አፈፃፀም ላሳዮ ዳኞች ተጫዋቾች እንዲሁም አስተዋፅዖ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ በአማረ መንገሻ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ