የኢንተር ሚያሚን ማለያ ለብሶ ፎቶ በመነሳቱ የኢንተርሚያምን ጨዋታ እንዳይመራ የተከለከሉ ዳኛ
ከሰሞኑ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በአሜሪካው ሜጀር ሊግ ሶከር ኢንተር ሚያሚ ከኦርላንዶ ሲቲ ጋር በነበረው ጨዋታ መርሐግብሩን እንዲመሩ የተመረጡት ዋና ዳኞች መነጋገሪያ ሆነዋል።
የፕሮፌሽናል ዳኞች ማህበር በቅድሚያ ጉይሄርሜ ሴሬታ የተሰኙ ዳኛ ለዚሁ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመድባቸዋል።
ግን ጨዋታው ሊጀመር ሰዓታት ሲቀሩት በጄሚ ሄሬራ ይቀየራሉ።
መጀመሪያ የተመደቡት የጨዋታ ዳኛ የተቀየሩበት ምክንያት የኢንተርሚያምን ማሊያ ለብሰው የተነሱት ፎቶ በማህበራዊ ትስስር ገፅ ሲዘዋወር በመታየቱ ነው።
በዕለቱ አራተኛ ዳኛ በመሆን ተመድበው የነበሩት ጄሚ ሄሬራ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት እንደሚሩት እና በእሳቸው ምትክ ኢቫን ሲድ ክሩዝ እንደመሩት ተደረገ።
ጨዋታውን ኢንተርሚያሚ ሉይዝ ሱዋሬዝ እና ሊዮኔል ሜሲ እያንዳንዳቸው ሁለት ጎል እንዲሁም ቴይለር አንድ ግብ በማከል ጨዋታውን 5ለዐ በሆነ ውጤት አሸንፎ መውጣቱ ይታወቃል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ