ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው በስልጢ ሀይቅ ዙሪያ የለማ ሙዝ ማሳ እየጎበኙ ነው

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው በስልጢ ሀይቅ ዙሪያ የለማ የሙዝ ማሳ እየጎበኙ ነው

ሀዋሳ: የካቲት 28/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የተመራ የክልሉ አመራር በስልጤ ዞን ምስራቅ ስልጢ ወረዳ ስልጢ ሀይቅ ዙሪያ የለማ ሙዝ ተመልክቷል::

በስልጢ ወረዳ የ30 40 30 ፕሮጀክት በ2014 ዓ.ም የተጀመሩ የተለያዩ ፍራፍሬዎች በክላስተር ለምተዋል::

በስልጢ ሀይቅ ዳርቻ ቀደም ሲል ባህር ዛፍ ተተክሎ የነበረ ሲሆን ባህር ዛፎችን በማንሳት ነው ከአንድ አመት በፊት በሙዝ ምርት የተተካው::

ባህር ዛፍን በሙዝ መተካት ያስፈለገበት ምክንያት ከሚኖረው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንፃር መሆኑን ለክልሉ አመራር ገለፃ ያደረጉት የምስራቅ ስልጢ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሳሎ ፋኒ ተናግረዋል::

25 ሄክታር መሬት ላይ ከለማው የሙዝ ምርት በተጨማሪ በ105 ሄክታር መሬት ላይ በአካባቢው ከለሙ ሌሎችም ፍራፍሬዎችም አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ ይገኛል ብለዋል::

በስልጢ ሀይቅ ዳርቻ የለማው ሙዝ የአይቻልምን አመለካከት የሚቀይር ነው ያሉት ደግሞ የስጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ከድር ናቸው::

በምስራቅ ስልጢ ወረዳ የታየውን ውጤታማ የሙዝ ልማት ሥራን በዞኑ በሚገኙ ሌሎች ወረዳዎችም ልምድ የማስፋት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል::

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው አካባቢው ላይ የታየው የሙዝ ልማት  አስደሳች መሆኑን ገልፀዋል::

በተጀመረው ትጋት በመቀጠል በሁሉም የልማት መስክ በክልሉ ብልፅግናን ለማረጋገጥ መስራት ይኖርብናል ብለዋል::

በመስክ ምልከታው ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ: ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ በብልፅግና  ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ  ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር: በምክል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም ከፍተኛ የክልሉ አመራሮች በመስክ ምልከታው ተሳትፈዋል::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ