የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች ጋር የዉይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በክልሉ ከሚገኙ የዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች ጋር የኑሮ ውድነትን ለመከላከልና በዘርፉ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና በመፍትሔዎች ዙሪያ የዉይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠዉ እንዳሉት፤ ክልሉ በዲስ መልክ ከተደራጀ ወዲህ በርካታ ስራዎችን ሲተገብርና ሲያከናዉን ቆይቷል።
በንግዱ ዘርፍ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ የንግዱ ማህበረሰብ ባለቤት ሆነው እንዲገለገል ለማድረግ በተሰራ ስራ የኦን ላይን አገልግሎት መስጠት ተችሏል።
መሰረታዊ የንግድ ስርዓት ማዘመን ዋነኛ መሆኑን በመግለፅ ስርዓቱ እንዳይዘምን የሚያደርጉ ማነቆዎችን መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ስልጤ ዞን ላይ 50 የሚሆኑ የዱቄት ፋብሪካዎች እንዳሉ በማንሳት አሁን ላይ 30 የሚሆኑት ብቻ ስራ ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
አክለውም ሁሉም ፋብሪካዎች በስራ ላይ እንዲዉሉና በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን በመለየት መፍትሄ በመስጠት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ቢሮው እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ይስሀቅ ማሶሬ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
በውይይት መድረኩ የዞንና ልዩ ወረዳ የንግድና ገበያ ልማት ተቋማት ኃላፊዎችና የዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ