የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች ጋር የዉይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በክልሉ ከሚገኙ የዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች ጋር የኑሮ ውድነትን ለመከላከልና በዘርፉ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና በመፍትሔዎች ዙሪያ የዉይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠዉ እንዳሉት፤ ክልሉ በዲስ መልክ ከተደራጀ ወዲህ በርካታ ስራዎችን ሲተገብርና ሲያከናዉን ቆይቷል።
በንግዱ ዘርፍ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ የንግዱ ማህበረሰብ ባለቤት ሆነው እንዲገለገል ለማድረግ በተሰራ ስራ የኦን ላይን አገልግሎት መስጠት ተችሏል።
መሰረታዊ የንግድ ስርዓት ማዘመን ዋነኛ መሆኑን በመግለፅ ስርዓቱ እንዳይዘምን የሚያደርጉ ማነቆዎችን መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ስልጤ ዞን ላይ 50 የሚሆኑ የዱቄት ፋብሪካዎች እንዳሉ በማንሳት አሁን ላይ 30 የሚሆኑት ብቻ ስራ ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
አክለውም ሁሉም ፋብሪካዎች በስራ ላይ እንዲዉሉና በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን በመለየት መፍትሄ በመስጠት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ቢሮው እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ይስሀቅ ማሶሬ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
በውይይት መድረኩ የዞንና ልዩ ወረዳ የንግድና ገበያ ልማት ተቋማት ኃላፊዎችና የዱቄት ፋብሪካ ባለቤቶች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው
መጪው ጠቅላላ ምርጫ ተአማኒና በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሣለኝ ገለፁ
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 28ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል