ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ሀላባ ዞን ገብተዋል
ሀዋሳ: የካቲት 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የተመራ የክልሉ አመራር ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ገብቷል:
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራው የክልሉ ከፍተኛ አመራር ቡድን በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ሲንብጣ ቀበሌ የመስኖ ልማት ሥራዎችን ተመልክቷል::
በቀበሌው በሶላር ሀይል በመታገዝ ሙዝ፣ ማንጎ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ አቡካዶ፣ ፓፓዬና ሌሎችም የጓሮ አትክልቶች ለምተዋል::
በመስክ ምልከታው ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ በምክል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም ከፍተኛ የክልሉ አመራሮች በመስክ ምልከታው ተሳትፈዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ