ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ሀላባ ዞን ገብተዋል
ሀዋሳ: የካቲት 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የተመራ የክልሉ አመራር ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ገብቷል:
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራው የክልሉ ከፍተኛ አመራር ቡድን በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ሲንብጣ ቀበሌ የመስኖ ልማት ሥራዎችን ተመልክቷል::
በቀበሌው በሶላር ሀይል በመታገዝ ሙዝ፣ ማንጎ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ አቡካዶ፣ ፓፓዬና ሌሎችም የጓሮ አትክልቶች ለምተዋል::
በመስክ ምልከታው ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ በምክል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም ከፍተኛ የክልሉ አመራሮች በመስክ ምልከታው ተሳትፈዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
ሀገራችንን ወደ ብልፅግና ለማድረስ የጽናት መንፈሳችንን ማደስ እንደሚገባ ተገለጸ
“ትንንሽ የሚመስሉ ስራዎች ለትልልቅ ዕድሎች በር ይከፍታሉ” – ወይዘሮ ህልውና ጌታቸው
የህግ ታራሚዎችን በስነ ምግባር ለማነፅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለፀ