በልማት ላይ በአርበኝነት መሥራት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ: የካቲት 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የተመራ የክልሉ አመራር በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ የግብርና ኢንቨስትመንት ልማት ሥራን ተመልክቷል::
በወረዳው በ10 ሄክታር መሬት ላይ በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የለማውን የበጋ መስኖ ስንዴና የጓሮ አትክልት የተመለከቱት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው አበረታች ሥራ ማየታቸውን ገልጸዋል::
በማሳው የታየውን መልካም ተሞክሮ በአቅራቢያ ባሉ አርሶ አደሮች እና በሌሎችም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባ አንስተዋል::
አባቶቻችን በአርበኝነት ሀገርን ጠብቀው አስተላልፈውልናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እኛም በግብርና፣ በጤና በትምህርትና በሌሎችም መስኮች ለትውልድ የሚበቃ የአርበኝነት ሥራ መፈፀም ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል::
ርዕሰ መስተዳድሩ የመስክ ምልከታው ዋና ዓላማ የግብርና እና የኢንቨስትመንት ሥራዎች ምን እንደሚመስሉ እንዲሁም ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በመስክ ላይ ለማየትና ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግ ነው ብለዋል::
በከምባታ ዞን ተዘዋውረው የተመለከቷቸው በኢንዱስትሪው እና በግብርናው ረገድ የተከናወኑ ተግባራትም ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል::
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እና ሌሎችም ከፍተኛ የክልሉ አመራሮች በመስክ ምልከታው ተሳትፈዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ