የአከባቢ ሰላምን ለማረጋገጥ የህብረተሰቡ ሚና ትልቅ ቦታ አለው – አቶ ተስፋዬ ይገዙ
ሀዋሳ፡ የካቲት 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት አባላት በክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር በህዝብ በተነሱ ጥያቄዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል ።
የህዝብ ተወካዮቹ ከህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመንግሥት አካላት አቅርበዋል ። የሚመለከታቸው አካላትም መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ በዚህ ወቅት እንደገለፁ የአከባቢውን ሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ግዴታውን ሊወጣ የገባል ብለዋል።
በክልሉ መሠረታዊ የመዋቅር ጥያቄዎች የተመለሱ በመሆኑ ህብረተሰቡ ፊቱን ወደ ልማት ብቻ እንዲያዞር ጥሪ አቅርበዋል ።
በክልሉ በርካታ ፕሮጀክቶች በከፍተኛ ወጪ ግንባታ ላይ ናቸው ያሉት አቶ ተስፋዬ፥ መንግስት የጀመራቸውን መጨረስ እንጂ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን የመጀመር ዕቅድ የለውም ብለዋል።
ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ግብርና የማምረቻው ዘርፍና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች የክልሉ ምጣኔ ሀብት መሠረት ለማድረግ ልዩ ዕቅድ መያዙንም ጠቁመዋል ።
በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠርና የተላላፊ በሽታዎችን ስጋት ለመግታት በትኩረት የክልሉ መንግስት እንደሚሰራ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል ።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ