የአከባቢ ሰላምን ለማረጋገጥ የህብረተሰቡ ሚና ትልቅ ቦታ አለው – አቶ ተስፋዬ ይገዙ
ሀዋሳ፡ የካቲት 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት አባላት በክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር በህዝብ በተነሱ ጥያቄዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል ።
የህዝብ ተወካዮቹ ከህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመንግሥት አካላት አቅርበዋል ። የሚመለከታቸው አካላትም መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ በዚህ ወቅት እንደገለፁ የአከባቢውን ሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ግዴታውን ሊወጣ የገባል ብለዋል።
በክልሉ መሠረታዊ የመዋቅር ጥያቄዎች የተመለሱ በመሆኑ ህብረተሰቡ ፊቱን ወደ ልማት ብቻ እንዲያዞር ጥሪ አቅርበዋል ።
በክልሉ በርካታ ፕሮጀክቶች በከፍተኛ ወጪ ግንባታ ላይ ናቸው ያሉት አቶ ተስፋዬ፥ መንግስት የጀመራቸውን መጨረስ እንጂ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን የመጀመር ዕቅድ የለውም ብለዋል።
ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ግብርና የማምረቻው ዘርፍና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች የክልሉ ምጣኔ ሀብት መሠረት ለማድረግ ልዩ ዕቅድ መያዙንም ጠቁመዋል ።
በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠርና የተላላፊ በሽታዎችን ስጋት ለመግታት በትኩረት የክልሉ መንግስት እንደሚሰራ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል ።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ