ሁሉም ቤተ-እምነቶች ለሠላምና አንድነት ከመንግስት ጎን በመቆም ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
በአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ በተካሄደበት ወቅት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ እንደገለፁት ሙስሊሙ ማህብረሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ለሠላም የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአሪ ዞንና ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ማታዶ በርቢ እና የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መላኩ አበራ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ሠላምና አንድነት ከሁሉም ልማት የሚቀድም ተግባር በመሆኑ ሁሉም ቤተ-እምነቶች በዚህ ልክ ጠንክረው ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተመሰረተው የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሠላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት የበኩሉን የማይተካ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የመንግስት የሥራ ሀላፊዎቹ አሳስበዋል።
የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጀማል መሐመድ በዞኑ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚመሰረቱ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶች ለሠላም ጠንክረው እንደሚሰሩ ገልፀው ማንኛውም የውስጥ ችግር ካለ በእነዚህ መዋቅሮች በንግግር የሚፈታ ይሆናል ብለዋል።
በምስረታው በጂንካ ከተማ አስተዳደር የሚሠሩ አካላት የተሰየሙ ሲሆን የተመረጡ አባላትም ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ