ሁሉም ቤተ-እምነቶች ለሠላምና አንድነት ከመንግስት ጎን በመቆም ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
በአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ በተካሄደበት ወቅት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ እንደገለፁት ሙስሊሙ ማህብረሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ለሠላም የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአሪ ዞንና ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ማታዶ በርቢ እና የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መላኩ አበራ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ሠላምና አንድነት ከሁሉም ልማት የሚቀድም ተግባር በመሆኑ ሁሉም ቤተ-እምነቶች በዚህ ልክ ጠንክረው ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተመሰረተው የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሠላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት የበኩሉን የማይተካ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የመንግስት የሥራ ሀላፊዎቹ አሳስበዋል።
የአሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጀማል መሐመድ በዞኑ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚመሰረቱ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶች ለሠላም ጠንክረው እንደሚሰሩ ገልፀው ማንኛውም የውስጥ ችግር ካለ በእነዚህ መዋቅሮች በንግግር የሚፈታ ይሆናል ብለዋል።
በምስረታው በጂንካ ከተማ አስተዳደር የሚሠሩ አካላት የተሰየሙ ሲሆን የተመረጡ አባላትም ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር