በፕሪሚዬርሊጉ ሀድያ ሆሳዕና መቻልን አሸነፈ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ16ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ ሃድያ ሆሳዕና መቻልን 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የሃድያ ሆሳዕና የማሸነፊያ ግቦችን መለሰ ሚሻሞ፥ግሩም ሃጎስ (በራሱ ላይ) እና ተመስገን ብርሃኑ አስቆጥረዋል።
ለመቻል አቤል ነጋሽ እና ከነዓን ማርክነህ ከሽንፈት መታደግ ያልቻሉ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል።
ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሀዋሳ ይጫወታሉ።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የእንግሊዝ ፕሪሚዬርሊግ አዲሱ የውድድር ዘመን ዛሬ ምሽት ይጀምራል
ማንቸስተር ሲቲ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫን አሸነፈ
ማንቸስተር ዩናይትድ ማቲያስ ዴሊትን ለማስፈረም ተስማማ