በፕሪሚዬርሊጉ ሀድያ ሆሳዕና መቻልን አሸነፈ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ16ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ ሃድያ ሆሳዕና መቻልን 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የሃድያ ሆሳዕና የማሸነፊያ ግቦችን መለሰ ሚሻሞ፥ግሩም ሃጎስ (በራሱ ላይ) እና ተመስገን ብርሃኑ አስቆጥረዋል።
ለመቻል አቤል ነጋሽ እና ከነዓን ማርክነህ ከሽንፈት መታደግ ያልቻሉ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል።
ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሀዋሳ ይጫወታሉ።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ
ጆሿ ዚርኪዜ በሮማ ይፈለጋል