በ800 ሜትር ሴት ኢትዮጵያን አትሌቶች ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዛሬ መካሄድ በጀመረው 19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴት ማጣሪያ ኢትዮጵያን አትሌቶች ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል።
ከምድብ አንድ ሀብታም አለሙ 2:00.50 1ኛ ስትወጣ፤ ከምድብ አራት ጽጌ ዱጉማ 2:00.50 በሆነ ሰዓት 1ኛ በመውጣት ሁለቱም ወደሚቀጥለው ውድድር አልፈዋል።
በሌላ በኩል በ800 ሜትር ወንድ ማጣሪያ መኮንን 1:49.71 በሆነ ሰዓት 5ኛ በመውጣት ወደሚቀጥለው ውድድር ማለፍ አልቻለም፡፡
ዘጋቢ፡ ሙለቀን ባሳ

More Stories
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል
8 ወራትን ብቻ በሰሜን ለንደን የቆየው አሰልጣኝ
ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን አሸነፈ