በ800 ሜትር ሴት ኢትዮጵያን አትሌቶች ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዛሬ መካሄድ በጀመረው 19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴት ማጣሪያ ኢትዮጵያን አትሌቶች ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል።
ከምድብ አንድ ሀብታም አለሙ 2:00.50 1ኛ ስትወጣ፤ ከምድብ አራት ጽጌ ዱጉማ 2:00.50 በሆነ ሰዓት 1ኛ በመውጣት ሁለቱም ወደሚቀጥለው ውድድር አልፈዋል።
በሌላ በኩል በ800 ሜትር ወንድ ማጣሪያ መኮንን 1:49.71 በሆነ ሰዓት 5ኛ በመውጣት ወደሚቀጥለው ውድድር ማለፍ አልቻለም፡፡
ዘጋቢ፡ ሙለቀን ባሳ
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ