በ800 ሜትር ሴት ኢትዮጵያን አትሌቶች ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዛሬ መካሄድ በጀመረው 19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴት ማጣሪያ ኢትዮጵያን አትሌቶች ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል።
ከምድብ አንድ ሀብታም አለሙ 2:00.50 1ኛ ስትወጣ፤ ከምድብ አራት ጽጌ ዱጉማ 2:00.50 በሆነ ሰዓት 1ኛ በመውጣት ሁለቱም ወደሚቀጥለው ውድድር አልፈዋል።
በሌላ በኩል በ800 ሜትር ወንድ ማጣሪያ መኮንን 1:49.71 በሆነ ሰዓት 5ኛ በመውጣት ወደሚቀጥለው ውድድር ማለፍ አልቻለም፡፡
ዘጋቢ፡ ሙለቀን ባሳ

More Stories
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ
ጆሿ ዚርኪዜ በሮማ ይፈለጋል