ዓድዋ ድል ለዘላቂ ሠላምና ለጠንካራ ሀገር መንግስት ግንባታ በሚል መሪ ቃል 128ኛው የአድዋ ድል በዓል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተከበረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓድዋ ድል ለዘላቂ ሠላምና ለጠንካራ ሀገር መንግስት ግንባታ በሚል መሪ ቃል 128ኛው የአድዋ ድል በዓል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተከብሯል።
የፕሮግራሙ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ እንዳሉት፤ በዓሉ በሀገሪቱ የሚፈጠሩ አንዳንድ የሀሳብ ልዩነቶችን በጋራ ለመፍታት የጋራ ምክክር የምናደርግበት ወቅት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
አድዋ የመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራትና በትብብር ድል የተቀዳጀንበት ቀን መሆኑንም አንስተዋል።
እኛ ስንተባበር ጠላቶቻችን ማሳፈር እንችላለን ያሉት ፕሬዝደንቱ ሀገርን ለማሻገር የጋራ ትብብር እና አንድነት ከምንም ቅድሚያ መሰጠት ያለበት ጉዳይ ነው ሲሉም አክለዋል።
በፓናል ውይይቱ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ፣ የዩኒቨርስቲ መምህራንና ተማሪዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የቀድሞ መከላከያ ሠራዊት አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ