ዓድዋ ድል ለዘላቂ ሠላምና ለጠንካራ ሀገር መንግስት ግንባታ በሚል መሪ ቃል 128ኛው የአድዋ ድል በዓል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተከበረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓድዋ ድል ለዘላቂ ሠላምና ለጠንካራ ሀገር መንግስት ግንባታ በሚል መሪ ቃል 128ኛው የአድዋ ድል በዓል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተከብሯል።
የፕሮግራሙ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ እንዳሉት፤ በዓሉ በሀገሪቱ የሚፈጠሩ አንዳንድ የሀሳብ ልዩነቶችን በጋራ ለመፍታት የጋራ ምክክር የምናደርግበት ወቅት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
አድዋ የመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራትና በትብብር ድል የተቀዳጀንበት ቀን መሆኑንም አንስተዋል።
እኛ ስንተባበር ጠላቶቻችን ማሳፈር እንችላለን ያሉት ፕሬዝደንቱ ሀገርን ለማሻገር የጋራ ትብብር እና አንድነት ከምንም ቅድሚያ መሰጠት ያለበት ጉዳይ ነው ሲሉም አክለዋል።
በፓናል ውይይቱ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ፣ የዩኒቨርስቲ መምህራንና ተማሪዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የቀድሞ መከላከያ ሠራዊት አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ