128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከበረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) 128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከብሯል።
በበዓሉ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ ወጣቱ ትውልድ ከአድዋ ድል ትምህርት በመውሰድ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ቁርጠኛ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።
የዲላ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሽፈራው በበኩላቸው አድዋ የብሔራዊ ክብር ማህተም የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል መሆኑን ጠቅሰው ለድሉ ምላሽ መስጠት የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ እንደሆነም አስገንዝበዋል።
በዓሉ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሐገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
ዘጋቢ : አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር