128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከበረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) 128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከብሯል።
በበዓሉ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ ወጣቱ ትውልድ ከአድዋ ድል ትምህርት በመውሰድ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ቁርጠኛ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።
የዲላ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሽፈራው በበኩላቸው አድዋ የብሔራዊ ክብር ማህተም የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል መሆኑን ጠቅሰው ለድሉ ምላሽ መስጠት የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ እንደሆነም አስገንዝበዋል።
በዓሉ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሐገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
ዘጋቢ : አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግርን በመቅረፍ የውሀ ሽፋኑን ለማሳደግ ከተለያዩ ተራድኦ ድርጅቶች ጋር እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል ሲከበር የእርሳቸውን አርዓያ በመከተል መልካም ተግባራትን በማከናወን ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የተሻሻለ የላም ዝሪያ በመጠቀም የወተት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ የጊምቦ ወረዳ አስተዳደር ገለጸ