128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከበረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) 128ኛው የአድዋ የድል በዓል በዲላ ከተማ ተከብሯል።
በበዓሉ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ ወጣቱ ትውልድ ከአድዋ ድል ትምህርት በመውሰድ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ቁርጠኛ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።
የዲላ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሽፈራው በበኩላቸው አድዋ የብሔራዊ ክብር ማህተም የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል መሆኑን ጠቅሰው ለድሉ ምላሽ መስጠት የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ እንደሆነም አስገንዝበዋል።
በዓሉ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሐገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
ዘጋቢ : አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ