የስደተኞች ጀልባ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አለፈ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወደ አውሮፓ ለመሻገር ጉዞ የጀመሩ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ በሴኔጋል ሰሜናዊ ክፍል በሚገኝ ባህር ውስጥ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
አፍሪካዊያን ስደተኞች ጀልባዋን ተሳፍረው ጉዞ ከጀመሩ ሳምንት እንዳለፋቸው ተገልጿል፡፡
ስደተኞቹ በሴኔጋል ባህር ከሰጠሙ በኋላ በባህሩ ላይ የ20 ሰዎች አስከረን ተገኝቷል ብለዋል የሀገሪቱ ባለሥልጣናት፡፡
የህይወት አድን ሠራተኞች የ20 ሰዎችን ሕይወት ማዳን መቻላቸውም ነው የተገለፁት ፡፡
ጀልባዋ ሴኔጋልን ለቃ ስትወጣ ከ200 እስከ 300 የሚጠጉ ስደተኞችን አሳፍራ ነበር ጉዞ የጀመረችው፡፡
የሴኔጋል ባህር ዳርቻ ስፔን ደሴት ደርሰው ወደ አውሮፓ ለሚሻገሩ አፍሪካዊያን ስደተኖች ሁነኛ ስፍራ ነው ሲል ቲአርቲ ዘግቧ፡፡
አዘጋጅ፡ መስከረም አበበ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ