የስደተኞች ጀልባ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አለፈ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወደ አውሮፓ ለመሻገር ጉዞ የጀመሩ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ በሴኔጋል ሰሜናዊ ክፍል በሚገኝ ባህር ውስጥ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
አፍሪካዊያን ስደተኞች ጀልባዋን ተሳፍረው ጉዞ ከጀመሩ ሳምንት እንዳለፋቸው ተገልጿል፡፡
ስደተኞቹ በሴኔጋል ባህር ከሰጠሙ በኋላ በባህሩ ላይ የ20 ሰዎች አስከረን ተገኝቷል ብለዋል የሀገሪቱ ባለሥልጣናት፡፡
የህይወት አድን ሠራተኞች የ20 ሰዎችን ሕይወት ማዳን መቻላቸውም ነው የተገለፁት ፡፡
ጀልባዋ ሴኔጋልን ለቃ ስትወጣ ከ200 እስከ 300 የሚጠጉ ስደተኞችን አሳፍራ ነበር ጉዞ የጀመረችው፡፡
የሴኔጋል ባህር ዳርቻ ስፔን ደሴት ደርሰው ወደ አውሮፓ ለሚሻገሩ አፍሪካዊያን ስደተኖች ሁነኛ ስፍራ ነው ሲል ቲአርቲ ዘግቧ፡፡
አዘጋጅ፡ መስከረም አበበ

More Stories
ብሔራዊ ምክክር ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባሻገር ችግሮችን በውይይትና በሀሳብ የበላይነት ለመፍታት መሠረት እንደሚጥል ተገለጸ
የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻ የማሳ ዝግጅት ቢያደርጉም በቂ ግብዓት አለማግኘታቸውን ገለጹ