የስደተኞች ጀልባ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አለፈ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወደ አውሮፓ ለመሻገር ጉዞ የጀመሩ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ በሴኔጋል ሰሜናዊ ክፍል በሚገኝ ባህር ውስጥ ሰጥማ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
አፍሪካዊያን ስደተኞች ጀልባዋን ተሳፍረው ጉዞ ከጀመሩ ሳምንት እንዳለፋቸው ተገልጿል፡፡
ስደተኞቹ በሴኔጋል ባህር ከሰጠሙ በኋላ በባህሩ ላይ የ20 ሰዎች አስከረን ተገኝቷል ብለዋል የሀገሪቱ ባለሥልጣናት፡፡
የህይወት አድን ሠራተኞች የ20 ሰዎችን ሕይወት ማዳን መቻላቸውም ነው የተገለፁት ፡፡
ጀልባዋ ሴኔጋልን ለቃ ስትወጣ ከ200 እስከ 300 የሚጠጉ ስደተኞችን አሳፍራ ነበር ጉዞ የጀመረችው፡፡
የሴኔጋል ባህር ዳርቻ ስፔን ደሴት ደርሰው ወደ አውሮፓ ለሚሻገሩ አፍሪካዊያን ስደተኖች ሁነኛ ስፍራ ነው ሲል ቲአርቲ ዘግቧ፡፡
አዘጋጅ፡ መስከረም አበበ

More Stories
በንድፈ ሃሳብ ደረጃ የተሰጣቸው ሥልጠና በተግባር የታጀበ መሆኑ በቀጣይ ለሚከናወነው ሥራ ውጤታማነት እንደሚያግዝ የዳዉሮ ዞን 3ኛ ዙር ሰልጣኝ አመራሮች ተናገሩ
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ