“በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ”- ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀድሞ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት አሊ ሀሰን ሙዊኒይ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ስም ገልጸዋል፡፡
“የዛሬው የሁለትዮሽ ውይይት ለዛሬው ጠንካራ ግንኙነታችን መንገድ የከፈተውን ታሪካዊ ትስስራችንን ያመላከተ ነበር። ዛሬ በግብርና፣ በኃይል ንግድ እና በባህል ትብብር የተፈራረምናቸው የመግባቢያ ሰነዶች ለቀጠለው እና ተናባቢ ለሆነው የልማት ስራችን መሰረት ናቸው።” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል፡፡
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል