“በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ”- ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀድሞ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት አሊ ሀሰን ሙዊኒይ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ስም ገልጸዋል፡፡
“የዛሬው የሁለትዮሽ ውይይት ለዛሬው ጠንካራ ግንኙነታችን መንገድ የከፈተውን ታሪካዊ ትስስራችንን ያመላከተ ነበር። ዛሬ በግብርና፣ በኃይል ንግድ እና በባህል ትብብር የተፈራረምናቸው የመግባቢያ ሰነዶች ለቀጠለው እና ተናባቢ ለሆነው የልማት ስራችን መሰረት ናቸው።” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል፡፡

More Stories
የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ህልውናን ለማስጠበቅ ይሰራል – የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ
የቃል ኪዳን ቤተሰብ ምስረታ ለዘላቂ ሠላም ግንባታ ጉልህ ፋይዳ መኖሩን የሠላም ሚኒስቴር ገለፀ
የሴቶችና ህፃናት ጥቃት ለመከላከል ቅድሚያ ከራስ መጀመር እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ ገለፁ