“በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ”- ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ የካቲት 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በታንዛኒያ የሀዘን ጊዜ ደማቅ በሆነ አቀባበል በሀገራቸው የተቀበሉኝን ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉህን አመሰግናለሁ ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀድሞ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት አሊ ሀሰን ሙዊኒይ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ስም ገልጸዋል፡፡
“የዛሬው የሁለትዮሽ ውይይት ለዛሬው ጠንካራ ግንኙነታችን መንገድ የከፈተውን ታሪካዊ ትስስራችንን ያመላከተ ነበር። ዛሬ በግብርና፣ በኃይል ንግድ እና በባህል ትብብር የተፈራረምናቸው የመግባቢያ ሰነዶች ለቀጠለው እና ተናባቢ ለሆነው የልማት ስራችን መሰረት ናቸው።” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል፡፡

More Stories
በ25 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የማሪ ቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል በርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት አባል በመሆናቸው ከድንገተኛ ህክምና ወጪ መዳን እንዳስቻላቸው ተገልጋዮች ገለጹ
ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የኢሠራ ባሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መሠረተ ድንጋይ አስቀምጧል