የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስፖርት ምክር ቤት የ1ኛ ዙር መስራች ጉባኤውን በወላይታ ሶዶ ከተማ ማካሄድ ጀመረ
የስፖርት ምክር ቤትቱ የ2015 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀሙንም እየገመገመ ነው ።
በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስፖርት ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ይገዙን ጨምሮ የፌደሬሽንና የስፖርት ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም የክልልና የዞን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በአዲሱ ክልል የመጀመሪያ ዙር መስራች ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ምክር ቤቱ አደረጃጀቱን የሀብት አሰባሰብን የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎችን እንዲሁም ውድድርና የስልጠና ማዕከላት ግንባታ ላይ የታዩ ለውጦች ይገመገማሉ።
በዕለቱ የደቡብ ኢትዮጵያ የስፖርት ምክር ቤት ማቋቋሚያ የመተዳደሪያ ደንብን ጨምሮ የውሎ አበል የሙያ አበልና የላብ መተኪያ ክፍያዎች መመሪያ ይፀድቃል።
ዘጋቢ ፡ ባዬ በልስቲ
More Stories
የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግርን በመቅረፍ የውሀ ሽፋኑን ለማሳደግ ከተለያዩ ተራድኦ ድርጅቶች ጋር እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል ሲከበር የእርሳቸውን አርዓያ በመከተል መልካም ተግባራትን በማከናወን ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የተሻሻለ የላም ዝሪያ በመጠቀም የወተት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ የጊምቦ ወረዳ አስተዳደር ገለጸ