የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስፖርት ምክር ቤት የ1ኛ ዙር መስራች ጉባኤውን በወላይታ ሶዶ ከተማ ማካሄድ ጀመረ
የስፖርት ምክር ቤትቱ የ2015 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀሙንም እየገመገመ ነው ።
በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስፖርት ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ይገዙን ጨምሮ የፌደሬሽንና የስፖርት ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም የክልልና የዞን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በአዲሱ ክልል የመጀመሪያ ዙር መስራች ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ምክር ቤቱ አደረጃጀቱን የሀብት አሰባሰብን የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎችን እንዲሁም ውድድርና የስልጠና ማዕከላት ግንባታ ላይ የታዩ ለውጦች ይገመገማሉ።
በዕለቱ የደቡብ ኢትዮጵያ የስፖርት ምክር ቤት ማቋቋሚያ የመተዳደሪያ ደንብን ጨምሮ የውሎ አበል የሙያ አበልና የላብ መተኪያ ክፍያዎች መመሪያ ይፀድቃል።
ዘጋቢ ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ