የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ ስኮትላንድ ተሸኘ
በ19ኛዉ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያን በመወከል የሚሳተፈው የአትሌቲክስ ልዑክ ቡድን እኩለ ቀን ላይ ውድድሩ ወደሚካሄድበት ግላስኮው ሲያቀና በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አሸኛኘት ተደርጎለታል።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ እና የፌደሬሽኑ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንግዳ ተገኝተዋል።
የፊታችን አርብ መካሄድ በሚጀምረው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ8 ሴት እና በ6 ወንድ አትሌቶች ትወከላለች።
ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ ከሁለት ዓመት በፊት በሰርቢያ ቤልግሬድ ላይ በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር ላይ 4 ወርቅ፣ 3 ብር እና 2 ነሃስ በድምሩ 9 መዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም አንደኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ