የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ ስኮትላንድ ተሸኘ
በ19ኛዉ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያን በመወከል የሚሳተፈው የአትሌቲክስ ልዑክ ቡድን እኩለ ቀን ላይ ውድድሩ ወደሚካሄድበት ግላስኮው ሲያቀና በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አሸኛኘት ተደርጎለታል።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ እና የፌደሬሽኑ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንግዳ ተገኝተዋል።
የፊታችን አርብ መካሄድ በሚጀምረው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ8 ሴት እና በ6 ወንድ አትሌቶች ትወከላለች።
ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ ከሁለት ዓመት በፊት በሰርቢያ ቤልግሬድ ላይ በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር ላይ 4 ወርቅ፣ 3 ብር እና 2 ነሃስ በድምሩ 9 መዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም አንደኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል እንግሊዝ ወደ ፍፃሜ ባለማለፏ ከፍተኛ ትችትን አስተናገዱ
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ