በአፍሪካ አገር አቋራጭ በወጣት ሴት ዘርፍ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ-5ኛ ደረጃ ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
ሀዋሳ፡ የካቲት 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአፍሪካ አገር አቋራጭ በወጣት ሴት ዘርፍ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ-5ኛ ደረጃ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል፡፡
በቱኒዚያ ሃማማት በመካሄድ ላይ በሚገኘው 6ኛዉ የአፍሪካ አገር አቋራጭ ሻምፒዮና በወጣት ሴት 6 ኪሎ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ-5ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን ሮቤ ዲዳ በአንደኝነት፣ የኔነሽ ሽመክት 2ኛ፣ ትነበብ አስረስ 3ኛ፣ መቅደስ ዓለምእሸት 4ኛ እና ኮከቤ አበራ 5ኛ በመውጣት ርቀቱን በበላይነት ማጠናቀቅ ችለዋል።
በሌሎች ርቀቶች በአዋቂ ሴት 10 ኪሎ ሜትር ደጊቱ አዝመራ ደረጃን በመያዝ ስታጠናቅቅ፥ በአዋቂ ወንድ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ገመቹ ዲዳ 3ኛ ወጥቷል።
በወጣት ወንድ 8 ኪሎ ሜትር ሃጎስ እዮብ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የጎዳና ሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል