የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

‎ሀዋሳ፡ የካቲት 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

‎የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ ጉባኤውን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፥ ምክር ቤቱ በሚኖረው የሁለት ቀናት ቆይታ በ5 የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ብለዋል።

‎በጉባኤው የ2018 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ለምክር ቤቱ እያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይ ዝርዝር ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

‎ምክር ቤቱ አስቀድሞ የ6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ የጀመረ ሲሆን፥ በግብርና፣ በመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በስራ እድል ፈጠራና በገቢ አሠባሰብ እንዲሁም በሌሎች ሴክተሮች አፈጻጸም ዙሪያ በተከናወኑ የልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ይመክራል።

‎6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ለሁለት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን ከወጣው መርሐ ግብር መረዳት ተችሏል።

‎ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ