የተማሪዎች ምገባ መጀመር ተማሪዎች በአግባቡ ትምህርት አንዲከታተሉ አስችሏል- የሣላማጐ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት
የሳላማጐ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባንታየሁ መለሰ እንደገለጹት በአለም ምግብ ኘሮግራም በወረዳዉ 24 ትምህርት ቤቶች መደበኛ እና ፍሬሽ ምግቦችን የሚጠቀሙ ሲሆን በአጠቃላይ ወንድ 5ሺ 394 ሴት 4 ሺህ 8 62 በድምሩ 10 ሺህ 256 ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የሃና መጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ሣይክል ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ተሻገር ወርቁ የዚህ ኘሮግራም መጀመር በትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ስራን ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ቤቱ የሒሳብ አስተማሪ የሆኑት መምህር ማሙሽ ጥጋቡም የዚህ ምገባ ኘሮግራም መጀመር በትምህርት ቤቱ የተማሪ ዉጤት ላይ መሻሻል መታየቱን ተናግረዋል፡፡
ተማሪ ልዩ ሳካና ተማሪ ብዙአየሁ አልማየሁ በጋራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ በፊት በተለያዩ ምክንያቶች ሳይመገቡ መተው እንደሚጨነቁና ለትምህርታቸው ትኩረት እንደማይሰጡ ገልፀው አሁን ግን በአግባቡ እየተከታተሉ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡
ዘጋቢ፡ደፋሩ ስፍታዬ- ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻ የማሳ ዝግጅት ቢያደርጉም በቂ ግብዓት አለማግኘታቸውን ገለጹ
ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የህዝብና የመንግስት አገልግሎቶችን የሚያፋጥን በመሆኑ ለሁሉም ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ