የተማሪዎች ምገባ መጀመር ተማሪዎች በአግባቡ ትምህርት አንዲከታተሉ አስችሏል- የሣላማጐ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት
የሳላማጐ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባንታየሁ መለሰ እንደገለጹት በአለም ምግብ ኘሮግራም በወረዳዉ 24 ትምህርት ቤቶች መደበኛ እና ፍሬሽ ምግቦችን የሚጠቀሙ ሲሆን በአጠቃላይ ወንድ 5ሺ 394 ሴት 4 ሺህ 8 62 በድምሩ 10 ሺህ 256 ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የሃና መጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ሣይክል ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ተሻገር ወርቁ የዚህ ኘሮግራም መጀመር በትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ስራን ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ቤቱ የሒሳብ አስተማሪ የሆኑት መምህር ማሙሽ ጥጋቡም የዚህ ምገባ ኘሮግራም መጀመር በትምህርት ቤቱ የተማሪ ዉጤት ላይ መሻሻል መታየቱን ተናግረዋል፡፡
ተማሪ ልዩ ሳካና ተማሪ ብዙአየሁ አልማየሁ በጋራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ በፊት በተለያዩ ምክንያቶች ሳይመገቡ መተው እንደሚጨነቁና ለትምህርታቸው ትኩረት እንደማይሰጡ ገልፀው አሁን ግን በአግባቡ እየተከታተሉ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡
ዘጋቢ፡ደፋሩ ስፍታዬ- ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ