የየም ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 18/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የየም ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ መካሔድ ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ በተለዩ ሁለት አጀንዳዎች ዙሪያ የመከረ ሲሆን፥ የ5ኛ ዙር 8ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ፣ የ1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን መርምሮ አጽድቋል።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ዝናሽ ገ/ስላሴ፥ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ፣ በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና በመንግሥት አሠራር ውስጥ የህዝብ ተሳትፎን በማረጋገጥ በህብረተሰቡ ኑሮ፣ መብትና ነጻነት ላይ አዎንታዊ ለውጥና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የሚያደርጉ አውራ ተቋማት ናቸው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን አሠፋ የዞኑን እጩ አስተዳዳሪ ለምክር ቤት አቅርበዋል።
በዚህ መሠረት የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩትን አቶ ሳሙኤል ገ/ሚካኤል በማንሳት አቶ ሽመልስ እጅጉን ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
ከዚህ በተጨማሪ አዲሱ የዞኑ አስተዳዳሪ ተጨማሪ እጩ ተሿሚዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
በዚህ መሠረት አቶ ገበየሁ ማሞ ኪያን ምክትል አስተዳዳሪና የሠላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ፣ ማዕረግ መኮንን የስራ ዕድል ፈጠራ ኤጀንሲ ኃላፊ እና ቴዎድሮስ ገዝሙን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አድርጎ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ
More Stories
የደመወዝ ማሻሻያውን ምክንያት በማድረግ ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ንግድ ቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ በዳውሮ ዞን የዋካ ከተማ አስተዳደር ንግድ ዩኒቲ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ35 ሺህ 4 መቶ ሄክታር በላይ የተጎዱ መሬቶችን በአርሶ አደር መር የተፈጥሮ ሀብት ማገገሚያ ዘዴዎች እያከናወነ መሆኑን ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አስታወቀ
በተፈጥሮ የሚከሰተውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ለመቀነስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ጥናትና ምርምር ለማድረግ ማቀዱን ገለፀ