በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ማቴዎስ አኒዮ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አድርገው ሾመ
ሀዋሳ፡ የካቲት 18/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ማቴዎስ አኒዮ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አድርገው ሾሟል::
አቶ ማቴዎስ አኒዮ ከወረዳ እስከ ክልል ባሉ በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ባገለገሉበት ወቅት በብቃትና በታማኝነት ማገልገላቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፖርቲ አቶ ይግለጡ አብዛ ገልፀዋል፡፡
በዚሁ መሰረት ጉባኤውም አቶ ማቴዎስ አኒዮን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
ዘጋቢ፡ በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ለወንጀል ድርጊት አመቺ የሆኑ ቦታዎችን በመቃኘት በአካባቢው ያለውን ሠላም በዘላቂነት ለማስቀጠል እየተሠራ ነው – የዲላ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት
የዘይሴ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ ” ቡዶ ከሶ” በዓል በድምቀት ተከበረ
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የተከተሉት የሰከነ የፖለቲካ ትግል ስልት በአርዓያነት የሚወሰድ መሆኑ ተገለጸ