የከምባታ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ የካቲት 18/2016 ዓ፣ም (ደሬቴድ) የከምባታ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ አስቸኳይ ጉባኤው ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
የዞኑ ምክር ቤት ባካሄደው በአስቸኳይ ስብሰባው ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ አስተዳዳሪ እንዲሆኑ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው ዶ/ር ዳዊት ለገሰ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ ኤክስኪዩቲቭ ቺፍ ዳይሬክተር፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ኮሌጅ ተባባሪ ዲን፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች አስተባባሪ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ ትምህርት ክፍል አስተባባሪ፣ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ሬጅስትራር እንዲሁም በዋቸሞ እና በሀዋሳ ዩኒቨርስቲዎች የ1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎችን በማስተማር መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በምክር ቤቱ ቀርበው ቃለ መሃላ የፈፀሙት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዳዊት ለገሰ ባደረጉት ንግግር ዞኑ ያለውን ፀጋ በመጠቀም ለነዋሪው የተሻለ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ በገቢ፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና እንዲሁም በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ አቶ ተክሌ ስዩም የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ እና አቶ ተሻለ ዩሐንስን ምክትል አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
ዘጋቢ፡ ቃልአብ ፀጋዬ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር