የከምባታ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ የካቲት 18/2016 ዓ፣ም (ደሬቴድ) የከምባታ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ አስቸኳይ ጉባኤው ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
የዞኑ ምክር ቤት ባካሄደው በአስቸኳይ ስብሰባው ዶ/ር ዳዊት ለገሰን የዞኑ አስተዳዳሪ እንዲሆኑ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው ዶ/ር ዳዊት ለገሰ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ ኤክስኪዩቲቭ ቺፍ ዳይሬክተር፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ኮሌጅ ተባባሪ ዲን፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች አስተባባሪ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ ትምህርት ክፍል አስተባባሪ፣ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ሬጅስትራር እንዲሁም በዋቸሞ እና በሀዋሳ ዩኒቨርስቲዎች የ1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎችን በማስተማር መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በምክር ቤቱ ቀርበው ቃለ መሃላ የፈፀሙት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዳዊት ለገሰ ባደረጉት ንግግር ዞኑ ያለውን ፀጋ በመጠቀም ለነዋሪው የተሻለ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ በገቢ፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና እንዲሁም በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ አቶ ተክሌ ስዩም የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ እና አቶ ተሻለ ዩሐንስን ምክትል አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟል።
ዘጋቢ፡ ቃልአብ ፀጋዬ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ