በኢፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ የካቲት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 49 አባላት አርባምንጭ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወሮ ፀሐይ ወራሳ እና በጋሞ አባቶች የተመራ ልዑክ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ተወካዮቹ በቀጣይ ወደ ምርጫ ክልላቸው በመሄድ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
የህዝብ ተወካዮች ከመረጧቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች በዓመት 2 ጊዜ ውይይት እንዲያደርጉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ይደነግጋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የፍትህ ተቋማት ተገልጋዩን ህብረተሰብ በሚመጥን መልኩ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ
በተገልጋይ እርካታና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ
የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑ ተጠቆመ