በኢፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ የካቲት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 49 አባላት አርባምንጭ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወሮ ፀሐይ ወራሳ እና በጋሞ አባቶች የተመራ ልዑክ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ተወካዮቹ በቀጣይ ወደ ምርጫ ክልላቸው በመሄድ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
የህዝብ ተወካዮች ከመረጧቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች በዓመት 2 ጊዜ ውይይት እንዲያደርጉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ይደነግጋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻ የማሳ ዝግጅት ቢያደርጉም በቂ ግብዓት አለማግኘታቸውን ገለጹ
ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የህዝብና የመንግስት አገልግሎቶችን የሚያፋጥን በመሆኑ ለሁሉም ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ