በኢፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ የካቲት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 49 አባላት አርባምንጭ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወሮ ፀሐይ ወራሳ እና በጋሞ አባቶች የተመራ ልዑክ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ተወካዮቹ በቀጣይ ወደ ምርጫ ክልላቸው በመሄድ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
የህዝብ ተወካዮች ከመረጧቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች በዓመት 2 ጊዜ ውይይት እንዲያደርጉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ይደነግጋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ