በኢፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ የካቲት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተመራጮች አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 49 አባላት አርባምንጭ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወሮ ፀሐይ ወራሳ እና በጋሞ አባቶች የተመራ ልዑክ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
ተወካዮቹ በቀጣይ ወደ ምርጫ ክልላቸው በመሄድ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
የህዝብ ተወካዮች ከመረጧቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች በዓመት 2 ጊዜ ውይይት እንዲያደርጉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ይደነግጋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የማሻ ከተማ ነዋሪዎች