“እኔ ለሃገሬ የሠላም ዘብ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በዲላ ከተማ የወጣቶች ውይይት መደረክ ተካሄደ

“እኔ ለሃገሬ የሠላም ዘብ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በዲላ ከተማ የወጣቶች ውይይት መደረክ ተካሄደ

ሀዋሳ፡ የካቲት 09/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “እኔ ለሃገሬ የሠላም ዘብ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ አባላት ለተጽዕኖ ፈጣሪ እና ለምሁራን ወጣቶች የተዘጋጀ የውይይት መደረክ አካሂዷል።

የውይይት መደረኩን በንግግር የከፈቱት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ፥ እንደ ሃገርም ሆነ እንደ ዞን በነበሩት እያንዳንዱ እንቅስቃሴዎች ወጣቶች ሲያበረክቱ የቆዩት አበርክቶ ከፍተኛ እንደነበረ ገልጸው፥ በአሁኑ ወቅትም ቢሆን ተሳትፎአቸውን ያላማከለ እንቅስቃሴ ውጤታማ ስለማይሆን ከወጣቶች ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢዩኤል ተሾመ ወጣቶች በማህበረሰቡ ውስጥ ወንድማማችነትንና እህታማማችነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ለሠላም ዘብ እንዲቆሙ አሳስበዋል።

በመድረኩም የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ሊግ አባላት ለተጽዕኖ ፈጣሪ አና ለምሁራን ወጣቶች የዞን፣ የክልልና የፓርቲው የወጣቶች ሊግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን