የ 2023/24 ዉድድር ዓመት የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ምሽት መካሄድ ይጀምራል

የ 2023/24 ዉድድር ዓመት የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ምሽት መካሄድ ይጀምራል

በ 8 ምድብ የተደለደሉ 32 ክለቦች የአንደኛ ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ እና ነገ ምሽት ያካሂዳሉ ።

በዛሬው እለት ከምድብ 5-8 የተደለደሉ ክለቦች የመክፈቻ መርሐ ግብራቸውን ያከናዉናሉ ።

በዚህ መሰረት

በምድብ አምስት ፦ 4:00 ፌይኖርድ ከ ሴልቲክ

4:00 ላዚዮ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ

በምድብ ስድስት ፦ 1:45 ኤሲ ሚላን ከ ኒዉካስትል

4:00 ፒኤስጂ ከ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ

በምድብ ሰባት ፦ 1:45 ያንግ ቦይስ ከ አርቢ ሌይፕዚች

4:00 ማንቸስተር ሲቲ ከ ሬድ እስታር ቤልግሬድ

በምድብ ስምንት ፦ 4:00 ባርሴሎና ከ ሮያል አንትዌርፕ

4:00 ሻክታር ዶኔስክ ከ ፖርቶ ይጫወታሉ ።

ለመጨረሻ ጊዜ በ 32 ቡድኖች በሚካሄደው በዘንድሮው የአዉሮፓ ሻምፒዎንስ ሊግ ዉድድር ፣ የጀርመኑ እግርኳስ ክለብ ኡኒየን በርሊን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፣ የእንግሊዙ ክለብ ኒዉካስትል ከ 20 ዓመታት በኋላ እንዲሁም አርሰናል ከ 6 ዓመታት በኋላ ይሳተፋሉ ።

የዚህ ዓመት የፍፃሜ ዉድድር በዌምብሌይ እንደሚካሄድ ያሳወቀው የአዉሮፓ እግርኳስ ማህበር ከሚቀጥለው የዉድድር ዓመት ጀምሮ የተሳታፊ ክለቦች ቁጥርም ወደ 36 ከፍ እንደሚል ማሳወቁ አይዘነጋም ።

አዘጋጅ ፡ ሙሉቀን ባሳ