የ 2023/24 ዉድድር ዓመት የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ምሽት መካሄድ ይጀምራል
በ 8 ምድብ የተደለደሉ 32 ክለቦች የአንደኛ ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ እና ነገ ምሽት ያካሂዳሉ ።
በዛሬው እለት ከምድብ 5-8 የተደለደሉ ክለቦች የመክፈቻ መርሐ ግብራቸውን ያከናዉናሉ ።
በምድብ አምስት ፦ 4:00 ፌይኖርድ ከ ሴልቲክ
4:00 ላዚዮ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ
በምድብ ስድስት ፦ 1:45 ኤሲ ሚላን ከ ኒዉካስትል
4:00 ፒኤስጂ ከ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ
በምድብ ሰባት ፦ 1:45 ያንግ ቦይስ ከ አርቢ ሌይፕዚች
4:00 ማንቸስተር ሲቲ ከ ሬድ እስታር ቤልግሬድ
በምድብ ስምንት ፦ 4:00 ባርሴሎና ከ ሮያል አንትዌርፕ
4:00 ሻክታር ዶኔስክ ከ ፖርቶ ይጫወታሉ ።
ለመጨረሻ ጊዜ በ 32 ቡድኖች በሚካሄደው በዘንድሮው የአዉሮፓ ሻምፒዎንስ ሊግ ዉድድር ፣ የጀርመኑ እግርኳስ ክለብ ኡኒየን በርሊን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፣ የእንግሊዙ ክለብ ኒዉካስትል ከ 20 ዓመታት በኋላ እንዲሁም አርሰናል ከ 6 ዓመታት በኋላ ይሳተፋሉ ።
የዚህ ዓመት የፍፃሜ ዉድድር በዌምብሌይ እንደሚካሄድ ያሳወቀው የአዉሮፓ እግርኳስ ማህበር ከሚቀጥለው የዉድድር ዓመት ጀምሮ የተሳታፊ ክለቦች ቁጥርም ወደ 36 ከፍ እንደሚል ማሳወቁ አይዘነጋም ።
አዘጋጅ ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ