የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ አርብቶ አደሮችና ነዋሪዎች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ፥ ኢትዮጵያ ያቀደችውን ግዙፍ ልማት ጀምራ ማጠናቀቅ እንደምትችል ማሳያ ነው ሲሉ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ አርብቶ አደሮችና ነዋሪዎች ገለፁ።
የግዱቡ ውሃ ሙሌት በተያዘለት የጊዜ ገደብ በመካሄዱ ደስተኞች መሆናቸውን ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጂንካ ቅርንጫፍ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዛሬ መንግስት የግድቡ የመጨረሻና አራተኛ ዙር ሙሌቱን ይፋ ማድረጉን በተለያየ መንገድ መስማታቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች በዚህም ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀዋል።
እጅ ለእጅ ከተያያዘንና አንድነታችንን ካጠናከርን ገና በርካታ ትላልቅ ልማቶችን ጀምረን መጨረስ የምንችል ህዝቦች መሆናችንን ለዓለም እናስመሰክራለን ሲሉም ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የግድቡ ቀሪ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚጠብቅብንን ድርሻ እንወጣለን፥ ሌላ ተጨማሪ ልማትም ጀምረን እንደ ህዳሴው ግድብ ሳናስተጓጉል እናጠናቅቃለን ሲሉም አቋማቸውን ገልፀዋል።
ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ