የቅጠል ቡና (ሀይታ ቱኬ)
በወላይትኛ “ሀይታ ቱኬ” ወይም የቅጠል ቡና በመባል የሚታወቀው በተለያዩ አካባቢዎች እንደ ቡና እና ሻይ ተዘውትሮ የሚጠጣ ባህላዊ ትኩስ የመጠጥ አይነት ነዉ።
ታዲያ ሀይታ ቱኬን ለማዘጋጀት እርጥብ የቡና ቅጠል፣ በሶብላ፣ ድምብላል፣ ነጭ ሽንኩርት፣ የጠጅ ሳር፣ አርቲ፣ ጤና አዳም፣ ዝንጅብል መሆናቸውን በወላይታ ሶዶ የቅጠል ቡና አዘጋጇ ወ/ሪት መሠረት ዘሪሁን ታስረዳለች፡፡
መጀመሪያ እርጥብ የቅጠል ቡና ተለቅሞ ከተወቀጠ በኋላ ፀሀይ ላይ እንዲደርቅ ይደረጋል፡፡ ከዚያም የሚበቃውን ያክል ዉሃ ተመጥኖ ይጨመርና ከፈላ በኋላ የቡናዉን ዉሃ እንዲጠል በማድረግ አንድ ላይ ከተወቀጡት ቅመማ ቅመሞች ጋር በማፍላት ለመጠጥነት ዝግጁ እንደሚሆን ታብራራለች።
የቅጠል ቡናው እንደየተጠቃሚው ምርጫ ለምግብነት ከተዘጋጀ ድንች፣ቦሎቄ፣ ቦዬ፣ ቦይና፣ እሸት በቆሎ፣ እና ከዳጣ ጋር ይቀርባል፡፡
ሀይታ ቱኬ ወይም የቅጠል ቡና በማንኛውም የዕድሜ ክልል ዉስጥ ያሉ ሰዎች የሚጠቀሙት ሲሆን ለጉፋን፣ ለብርድ፣ በቅዝቃዜ ወቅት ሙቀት ለማግኘት ፍቱን መሆኑ ይነገራል።
ሀይታ ቱኬ ቤተሰብ ወይም ጎረቤት ሰብሰብ ባሉበት ተዘጋጅቶ ከቁርስ ጋር በደራ ጨዋታው መካከል ወዳጅነትን የሚያደራጅ ባህላዊ ትኩስ መጠጥ ነው።
ወ/ሪት መሠረት ዘሪሁን እንዳሉት ወላይታ በእንግድነት ጎራ የሚሉ ሁሉ መንገድ ዳር ካሉ ምግቦች ጋር ከሚዘወተሩት ትኩስ መጠጦች ውስጥ ሀይታቱኬን እንዲቀምሱ በአስተያየታቸው ጠቁመዋል።
አዘጋጅ፡ ሐና በቀለ
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ