የቅጠል ቡና (ሀይታ ቱኬ)
በወላይትኛ “ሀይታ ቱኬ” ወይም የቅጠል ቡና በመባል የሚታወቀው በተለያዩ አካባቢዎች እንደ ቡና እና ሻይ ተዘውትሮ የሚጠጣ ባህላዊ ትኩስ የመጠጥ አይነት ነዉ።
ታዲያ ሀይታ ቱኬን ለማዘጋጀት እርጥብ የቡና ቅጠል፣ በሶብላ፣ ድምብላል፣ ነጭ ሽንኩርት፣ የጠጅ ሳር፣ አርቲ፣ ጤና አዳም፣ ዝንጅብል መሆናቸውን በወላይታ ሶዶ የቅጠል ቡና አዘጋጇ ወ/ሪት መሠረት ዘሪሁን ታስረዳለች፡፡
መጀመሪያ እርጥብ የቅጠል ቡና ተለቅሞ ከተወቀጠ በኋላ ፀሀይ ላይ እንዲደርቅ ይደረጋል፡፡ ከዚያም የሚበቃውን ያክል ዉሃ ተመጥኖ ይጨመርና ከፈላ በኋላ የቡናዉን ዉሃ እንዲጠል በማድረግ አንድ ላይ ከተወቀጡት ቅመማ ቅመሞች ጋር በማፍላት ለመጠጥነት ዝግጁ እንደሚሆን ታብራራለች።
የቅጠል ቡናው እንደየተጠቃሚው ምርጫ ለምግብነት ከተዘጋጀ ድንች፣ቦሎቄ፣ ቦዬ፣ ቦይና፣ እሸት በቆሎ፣ እና ከዳጣ ጋር ይቀርባል፡፡
ሀይታ ቱኬ ወይም የቅጠል ቡና በማንኛውም የዕድሜ ክልል ዉስጥ ያሉ ሰዎች የሚጠቀሙት ሲሆን ለጉፋን፣ ለብርድ፣ በቅዝቃዜ ወቅት ሙቀት ለማግኘት ፍቱን መሆኑ ይነገራል።
ሀይታ ቱኬ ቤተሰብ ወይም ጎረቤት ሰብሰብ ባሉበት ተዘጋጅቶ ከቁርስ ጋር በደራ ጨዋታው መካከል ወዳጅነትን የሚያደራጅ ባህላዊ ትኩስ መጠጥ ነው።
ወ/ሪት መሠረት ዘሪሁን እንዳሉት ወላይታ በእንግድነት ጎራ የሚሉ ሁሉ መንገድ ዳር ካሉ ምግቦች ጋር ከሚዘወተሩት ትኩስ መጠጦች ውስጥ ሀይታቱኬን እንዲቀምሱ በአስተያየታቸው ጠቁመዋል።
አዘጋጅ፡ ሐና በቀለ

More Stories
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ